>

አስደንጋጭ መረጃ ከተባበሩት መንግስታት የጸጥታ እና ደህንነት ዲፓርትመንት (አሰግድ ታመነ) 

የወልድያው ጭፍጨፋ ሆን ተብሎ፤ ታቅዶበት እና ሙሉ ዝግጅት ተደርጎበት በህዋሃት አማካኝነት የተፈጸመ ዘር ተኮር የበቀል ርምጃ ነው

አስደንጋጭ መረጃ ከተባበሩት መንግስታት የጸጥታ እና ደህንነት ዲፓርትመንት 

የምታዩት የኢሜል መልእክት የተላለፈው አዲስ አበባ ፤ ባህርዳር እና ሌሎች ዋና ዋና የሃገሪቱ ከተሞች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ካለው ከUnited Nations Department for Safety and Security ሲሆን ለተቋሙ ሰራተኞች በውስጥ በኩል የተላለፈ ኦፊሲያላዊ ማስታወሻ (official memo) ነው። ይህ ሚስጥራዊ መልዕክት የሚተላለፍላቸው በየቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ላሉ ዋና ዋና የጸጥታ ተወካዮች (security focal persons) ነው።

በዚሁ መልዕክት በግልጽ እንደተቀመጠው ለወልድያው ጭፍጨፋ መንስኤ ተደርጎ የተወሰደው በአማራ እና ትግራይ ብሄሮች መካከል ከወራት በፊት ጀምሮ በተከሰተ የፖለቲካ ችግር ምክንያት ነው ይልና በዋናነት ግን የጭፍጨፋው መንስኤ የኢትዮጵያ መንግስት የትግራይ መከላከያ ሃይሎችን በወልድያ ከተማ ማሰማራቱ እንደሆነ ያትታል“The Government deployed Tigrayan military forces to the area which triggered more resistance”

በህይወት እና ንብረት ላይ የደረሰውን ውድመት ከዘረዘረ በኋላ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታ እና ደህንነት ዲፓርትመንት በአማራ ክልል የሚደረጉ ተልዕኮዎችን በጊዚያዊነት እንዳገደ ይገልጻል። በጭፍጨፋው ምክንያት ትግራይ ክልል የሚኖሩ አማራዎች የበቀል ርምጃ ሊወስዱ ስለሚችሉ በመቀሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያሉ የWHO ሰራተኞች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ሲልም ያሳስባል።

እኛም ሰሞኑን ስንል የነበረው ይህንኑ ነው። የወልድያው ጭፍጨፋ ሆን ተብሎ፤ ታቅዶበት እና ሙሉ ዝግጅት ተደርጎበት በህዋሃት አማካኝነት የተፈጸመ ዘርተኮር የበቀል ርምጃ ነው።

(መልዕክቱ ትላንት ከተላለፈ በኋላ ለህዝብ እንዲደርስ በሚል ሙሉ መረጃውን የላኩልን በተባበሩ መንግስታት ድርጅት ውስጥ የሚሰሩ ወንድሞቻችን ናቸው! ጭፍጨፋውን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሰማውን ሀዘን ከጄኔቫ የገለጸበት ኦፊሳሊያዊ መልዕክትም እንዲሁ አብሮ ተልኳል! )

Filed in: Amharic