>
5:13 pm - Monday April 18, 3768

33 የፖለቲካ እስረኞች ከ15 እስከ 18 አመት ተፈረደባቸው

በጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በእነ ሚፍታህ ሸህ ሱሩር ክስ መዝገብ በግንቦት 7 የተከሰሱ 33 ግለሰቦች ላይ የፍርድ ውሳኔ ሰጥቷል። በክስ መዝገቡ 77ተከሳሾች ክስ የቀረበባቸው ሲሆን 33ቱ አምነው ሲከራከሩ ቆይተዋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥር 3/2010 ከሰዓት በኋላ በነበረው የችሎቱ የስራ ሰዓት በተከሳሾቹ ላይ ከ15 እስከ 18 አመት ቅጣት ወስኖባቸዋል። ቀሪዎቹ ተከሳሾች ክደው የተከራከሩ በመሆኑ የመከላከያ ምስክር ለማቅረብ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል።

Filed in: Amharic