ስለ ቤተመንግስቱ የ17 ቀን የኢህኣዲግ ስብሰባ የህውሓት አባላት በዝርዝር ይነገራቸዋል ምን እንዳጡ ምን እዳገኙ ማን እንደ ደገፍቸው ማን የተጋሩን ስልጣን ለመንጠቅ እንዳሰፈሰፈ ከመጀመርያ ቀን ውላቸው እስከ 17ተኛ ቀን የነበረው ሂደት ይተነተንላቸዋል ። እኛ ለህውሓት የስጋ ዘመዶች ስላልሆንን ስለ ዝጉ ስብሰባ እሚነግረንም የለም እንመራችሀለን የሚሉትም ሰወች የተወያዩበትን አጀንዳ ለህዝብ በይፍ ሲያወጡ አይታይም ። ለመጪው 8 ቀናት የ4ኪሎውን ቤተመንግስት ለሀይለማርያም በይደር ሰጥተው አዲስ አበባን ለአሰፍ አብዩ በአደራ አስይዘው የህውሓት መሪዎች ሰሜናዊት ኮከብ ይከትማሉ ።
በመጨረሻም ስለ እስረኛ ፍቺ በደንብ ይወያያሉ እሚፈቱት ታሳሪዎች ከእዛ መልስ ሊሆን ይችላል ተለይተው ሚታወቁት ። የህውሓት አባላት በሽብር የተከሰሱትን እስረኞች ማነው እንድንፈታ ያስገደደን የአለም ባንክ ፕሬዝዳንታ ነች ፣ ወይስ እምትደራደራቸው ፓርቲዎች አልያም ኦህዴድና ብአዴን ብለው በግልፅ ይጠይቃሉ ። ኦህዴድ ይሁን ብአዴን በሀገራዊ ጉዳይ ላይ የመወሰን ስልጣን እንደሌላቸው በተደጋጋሚ የታየ እውነት ሲሆን ህውሓት በዚህ ስብሰባ ላይ ለመጋቢቱ የሀዋሳ ኢህአዴግ ጉባኤ ላይ እሚሳተፍ አባላቱንም ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል ።
በመቐለ ስብሰባ ሳሞራና ስብሀት ስለ ትግራይ ህዝብ ሲባል እንዲግባቡ ይለመናሉ
ዘውዴ ታደሰ
Filed in: Amharic