ባህርዳር ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል ፤ የክልሉ ፖሊስና ልዩ ኃይል ቦታ ቦታቸውን እንደያዙ ቢሆንም መከላከያና ፌደራል ፖሊስ በእያንዳንዱ የመንደር መታጠፊያ ጭምር ተመድበዋል። ከትግራይ የተመደቡ ተማሪዎች በከተማው ወዳለው “አዲስ አምባ” ወደተባለ ትልቅ ሆቴል ተወስደው ጥበቃ እየተደረገላቸው መሆኑ ተነግሯል። ምስራቅና ምዕራብ ጎጃም በርካታ ኦራሎች ወታደር ጭነው በየወረዳው እየተሰማሩ ነው። ከብአዴን ለተሰነዘረው ቅሬታ ህወሓት በኢህአዴግ ፅ/ቤት በኩል ብሔራዊ መረጃና ደህንነት መስሪያ ቤት ከፍተኛ አደጋ እንደሚፈፀም የታጠቁ ኃይሎች ሰርገው መግባታቸውም መረጃ አለው የሚል ምላሽ በመስጠቱ በአንዳንድ የብአዴን አመራሮች ከቅሬታ ከፍ ያለ ተቃውሞ የገጠመው መሆኑ እየተሰማ ነው። ለሊቱን መከላከያና ፌደራል በርካታ ተማሪዎችና ወጣቶችን እያሰሩ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛዎች ለማጋዝ ማቀዳቸው ብርሸለቆ ድንኳኖች እየተተከሉ መሆኑ ተጠቁሟል።
ወሎ እና ጎጃም በዛሬ ውሎ (ሃብታሙ ኣያሌው)
Filed in: Amharic