>

አቁማዳ አሲዘህ በበተንከዉ ዘርህ መወራረድ ካሻህ፣ ከራስ ጠጉራችን ላይ፣ አንዱዋን ትነካለህ!!!!!! (ሃራ አብዲ)

በህልም ያላሰቡት፤ ስልጣን ገብቶ እጃቸዉ፤
የሚሆኑት አጡ፤ አክለፈለፋቸዉ፤
ባይን ያላዩት ምግብ፣ ሲገባ ካፋቸዉ፣
የትኛዉን ይብሉት፣ የቱ ይቅርባቸዉ።
ባቡጀዴ ሽርጥ፣ ጅብ አይበላሽ ጫማ፣
በድህነት አከዉ፣ ከበሩ ዛሬማ።
በላይ በላዩ ላይ፣ ምቾትን ሲጎርሱ፣
አንጀት አላነሱም፤ አልጠረቁ እነሱ፣
እንደምን አድርገዉ፣ ከማእዱ ይነሱ።

አይናቸዉ ሲሰስት፣ ባዩት ለምለም አፈር፣
አየናቸዉ ሲቀላ፣ ባዩት በጎ ነገር፣
እጃቸዉ ሲሰስት፣ በተሰረቀ ብር፣
ለሃጭ በለሃጭ ሆነ፤ የረገጡት ምድር።
በሃገር ያለዉን፣ ቢገድሉ ቢገርፉ፤
አልጠቅም ቢላቸዉ፤
በጠጡት የሰዉ ደም፣
ልጉዋሙ ቢበጠስ፤ የዞረዉ ናላቸዉ፤
ባህር ማዶ አሰቡ፤ ቅሌታሞች ናቸዉ።
በጆሮዉ ቀለበት፣ ባፉ ቅሌት ቅሞ፤
ህወሃት የሚሉት፣ ይህ የለማኝ መንጋ፣
ድንበር ተሻገረ፣ ሊሰልለን ደግሞ።
የገማ ስእብና፣ የከረፋ እብሪት፤
ከቶ እንዴት ሆነዉ ነዉ፣
ሰዉ ፊት የሚቆሙት።

የትግራይን ትዉልድ፣ መጪዉን በከሉት፣
ትግሬን አያድርገኝ፣ እንግዲህ ወደፊት።
ለማሰር፣ ለመግረፍ፣ ለመዝረፍ ለመግደል፤
ጠብመንጃዉ ይበቃል፣
ሀገር ማስተዳደር፤ ጠበብ ይጠይቃል፣
በወጉ ለመግዛት፤ ልብን ይጠይቃል፤
በሀገር ፣ በአለም፣ ሰላይ ብትበትን፣
ጥላህን ጠርጥረህ፤ ስትደነብር ብትዉል፣
አይገቡ አስገብተን፣ እናስተፋሃለን፣
ገና ያካበትከዉ፣ እሳት ይበላዋል፤
ፋሽስቱ ወያኔ !
በነቂስ ተለቅመህ፣ ፍዳህን ታያለህ፣
መሰለል ቀርቶብህ፣ ነፍስህን ከሰይፍ፣
ጭራህን ከእሳት፣ ማትረፍ በሆነልህ።
በመላዉ ኢትዮጵያ፣ አቁማዳ አሲዘህ፣
በበተንከዉ ዘርህ፤ መወራረድ ካሻህ፣
ከራስ ጠጉራችን ላይ፣ አንዱዋን ትነካለህ!!!!1

Filed in: Amharic