እኔ፣ ይህን ስርዓት የምነቅፈው፣ ሥራና አሰራሩን ዘወትር የምተቸው፣… ጠዋት ማታ የምፅፈው፣ የምናገረው፣ የማስበው፣ የዜጎች መብትና ነፃነት እንዲከበር ነው! “የአንድ ወገን የበላይነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የብዙሃኑ መብትና ነፃነት መጣስ የለበትም” ብዬ ስለማምን ነው። ይህ የአንዱ ብሔር ደጋፊ፣ የሌላው ብሔር ተቃዋሚ በመሆን ሳይሆን፣ “ሁሉም ሰው እንደ ሰው እኩል መብት፥ ነፃነትና ተጠቃሚነት ይገባዋል” የሚል ፅኑ እምነት ስላለኝ ነው። ነጋ ጠባ “የኦሮሞ ሕዝብ መብት ይከበር!” እያልኩ የምጮኸው የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን እንጂ ሰሞኑን በኢሊባቡርና በመቱ፣ ዛሬ ደግሞ በነቀምት እንደሆነው፣ በተለይ የአማራና የትግራይ ተወላጆች መንገድ ላይ ተደፍተው እንዲቀሩ አይደለም።
የኦሮሚያ