ቀዳሚ፤
እነሆ ከጣምራ ቁስል በፊት “ቀይ አንበሳ” ነበረ። እነሆም ስለ ‘ቀይ አንበሳ’ ‘በማንኪያ’ እናቀምሳለን። እንዲህ ብለን፤ አልኻንድሮ ዴል ባዬ ኩባዊ ነው። ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት ለንደን፤ እንግሊዝ ውስጥ ነበር። በወቅቱ በእንግሊዝ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ሀኪም ወርቅነህ ማርቲን (ደብሊው ማርቲን) በጋዜጣ ላይ ባወጡት ማስታወቂያ አነሳሽነት አምባሳደሩ ፊት በመቅረብ ለአትዮጵያ በፈቃደኝነት ለመዋጋት የሚፈልግ መሆኑን ይገልፃል። አምባሳደር ወርቅነህም ጠየቁት፤