>

ንዋይ እና ታማኝ [ሄኖክ የሺጥላ]

Tamagne-Beyene-Sisay-Agenaየንዋይ ዘማዮችን ቀልብ አስተው ከእግራቸው ስር ያንበረከኩ ዳንዴ ጀብራራዎች ሁሉም ንዋይ ይመስላቸዋል ። ታማኝነት ከንዋይነት እጅግ የተለየ ስለመሆኑ ስም የግብር ምልክት ነው ለሚለው አባባል ቅን እና ቀጥተኛ ምሳሌ ይመስለኛል ። ገንዘብ ሁሉንም እና ማንንም ይገዛል ብለው የሚያስቡ ፥ ከዚህ ቀደም በገዟቸው ሰለሞናዊ የሰው ኮርማዎች ልክ ቴዎድሮሳዊያንን ለመግዛት ሲሞክሩ ስናይ ፥ ግብራቸው ከመፃጉነት እና ከተስፋ ቢስነት የመነጫ ብናይ ጥረት እንደሆነ ለመገመት አይዳግተንም ። እጃቸው የሳት ሰደድ የሆኑትን በንዋይ መዳፍ ለመያዝ መሞከር የተሞካሪውን ማንነት አቅሎ ከማየትም የመነጨ አልቦ ምንነት ነው ባይ ነኝ።

እርግጥ ገንዘብ ኩንታል ጤፍ ይገዛ ይሆናል ፥ አንድ ጉርሻ ፍቅርን ግን አይገዛም ! እርግጥ ገንዘብ እልፍኝ ሙሉ ባለሟልን ያመጣ ይሆናል ፥ ግን ደሞ በልፍኙ ካሉ እልፍ ባለሟሎች ልቦና ውስጥ ፍቅር ንጦ ማውጣት አይቻለውም ። እርግጥ ገንዘብ ቤት እና መኪና ይገዛ ይሆናል ፥ የህሊና ሰላም ግን መግዛት አይቻለውም ፥ እርግጥ ገንዘብ ሃገር መግዛት ይችል ይሆናል የሃገር ፍቅር መፍጠር ግን አይቻለውም ፥ እርግጥ ገንዘብ ወርቅ መግዛት ይችል ይሆናል ፥ ወርቅ ትውልድን ማንበርከክ ግን አይቻለውም ።

በገንዘብ ልትገዙ የሞከራችሁት በገንዘብ የሚገዛ ነገርን አይደልም! ታማኝ ታማኝ ነው ስለዚህ ይታመናል ። ስሙም ግብሩም ንዋይ እና ንዋያዊ አይደለም ። ሲሳይ ሲሳይ ነው ፥ ለናንተ በረከት ቢሆናችሁ እንጂ ፥ ከህመማችሁ ቢያክማችሁ እንጂ የናንተን በረከት የሚፈልግ ሰው አይደለምና ። ሙሉ ሰዎችን በገንዘብ ማጉደል አይቻልም ።
የመንፈስ ሙሉነትን በንዋይ ማደፍረስም ሆነ ማፍሰስ አይቻልም ! እውነት በገንዘብ ቢገዛ ኖሮ ፥ እውነት የሚባል ነገር ባልኖረ! የእውነት ትልቅነት ንዋይንም ማለፍ መቻሉ ነው ! ታማኝ ቅዱስ ስም ነው ፥ ሲሳይ ቅዱስ ስም ነው ፥ ብፁዕ የሆኑት ግን በግብራቸው ነው!!!! ድል ለእውነተኛ የኢትዮጵያ ልጆች !

Filed in: Amharic