ከዲሲ ግብረ ሀይል የተሰጠ መግለጫ!
በኤኢሳ ዋን (AESA ONE) ላይ መሳተፍ በወገናችን እልቂት መቀለድ ነው !!
በዚህ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል በተዘጋጀ ዝግጅት ላይ ማንኛውም አገር ወዳድ ባለመካፈል ወገናዊነታችሁን እንድታሳዩ ጥሪአችንን እያስተላለፍን፤ በተጨማሪም አርቲስቶቻችንን ክብር የሰጣችሁ ወገናችሁን ፀረ ኢትዮጵያ በሆነ ዝግጅት ላይ ባለመካፈል አጋርነታችሁን አሳዩ እያልን፤ በዚህ የደም ዝግጅት ላይ የወገናችሁን እልቂት ችላ ብላችሁ በምትሳተፉ አርቲስቶች ላይ ማህበረሰቡ በማናቸውም ዝግጅቶቻችሁ ላይ ማእቀብ (boycott) እንደሚያደርግባችሁ ከወዲሁ ልትረዱት ይገባል ።
ይህንኑ ዝግጅትም በመቃወም በዲሲ እና አካባቢው የሚገኙ ሀገር ወዳዶች የተለያዩ የተቃውሞ ዝግጅቶች ያዘጋጁ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።
የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል!!!