>
5:14 pm - Tuesday April 20, 8551

ከኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን እና ሬዲዮ የተሰጠ መግለጫ

ታህሳስ 9/2008
December 19/2015

ESAT new satelitESAT new satelitየኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን እና ራዲዮ በኢትዮጵያ እና አካባቢዋ ሃገሮች በሁለት ሳተላይት ከሚያስተላልፋቸው ስርጭቶች አንዱ በሆነው Eutelsat E8WB @ 8 West ሳተላይት የሚያስተላልፈው ስርጭት ከቅዳሜ ታህሳስ 9/2008 /December 19/2015/ ማለዳ ጀምሮ እየታውከ ሲሆን፣በአንዳንድ አካባቢዎች ሙሉ ለሙሉ መቐረጡን አረጋግጠናል።የሁለተኛው ሳተላይት Eutelsat 70B @70.5 East ግን አሁንም ስርጭቱ በጥራት ቀጥሏል። የተቋረጠው ሳተላይት የችግሩ ምንጭ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ባለሙያዎች እና ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ የሚለቀው የአፈና ሞገድ መሆኑ የታወቀ ሲሆን፣በዚሀ ዓለም ኣቀፍ ህግን በተጻረረ ድርጊት ከኢሳት ባሻገር ሊሎች የውጭ ቴሌቪዥን ጣቢያዎችም ታውከዋል፡፡የኢሳት ማኔጅመንት እና የቴክኒክ ቡድን በጉዳዩ ላይ ከሳተላይት አቅራቢው ኩባንያ ጋር እየተነጋገረ ይገኛል።ኢሳት ስርጭቱን በዚሁ ሳተላይት ጭምር ለማስቀጠል ከሚያደረገው ጥረት ጎን ለጎን በተጨማሪ ሶስተኛ ሳተላይት ለማስተላለፍ የኢሳት የቴኪኒክ ቡድን እየሰራ ሲሆን፣ ተመልካቾቻችን በትዕግስት እንዲጠብቁን እየጠየቅን፣ እስከዚያው በሁለተኛው እና በሚከተለው ሳተላይት ስርጭቶቻችንን እንድትከታተሉን እንጠይቃለን።
Eutelsat 70B @70.5 East
Dawnlink – 11456.817 MHZ
Polarity- Horizontal
Symbol Rate 1700
FEC- 2/3
የኢሳት አስተዳደር

Filed in: Amharic