>

የትግራይ ሽፍቶች ለምን ወንድሞቻቸውን ይገድላሉ? [ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም]

የቼኩ ሪፐብሊኩ ተወላጂ የዚህ መጽሃፍ ደራሲ ኣዶስፍ ፕርለሳክ- ትርጉም ተጫነ ጆብሬ መኮንን

አፄ ምኒልክ ጦራቸውን ሰብስበው በእግርና በበቅሎ ከደቡብ ተነስተው ትግራይ እስቲደርሱ ኤርትራና ትግራይ ምን አድርገው ጠበቁዋቸው? የኢጣልያ ጦር ትግራይን ሰንጥቆ አምባ አላጌ እስቲደርስ ማን ሊያቆመምው ሞከረ? የኢጣሊያ ጦር መቀሌ ገብቶ ሲመሽግ ማን ተከላከለው? ስብሓት እስከዛሬ ሳይገለጥለት ቀርቶ ከሆነ የኢጣልያንን ጦር ከአምባ አላጌ ያስወጣው የምኒልክ ጦር ነው፡፡ ከመቀሌም ምሽግ ያስወጣው የጣይቱ ዘዴና የምኒልክ ጦር ነው፡፡ በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ተሸፋፍኖ የቆየውን እናፍረጥርጠው ከተባለ ለማን አሳፋሪ እንደሚሆን ግልጽ ነው፡፡
ስለአድዋው ጦርነት ምስክርነት የሚሰጠን ገለልተኛ ታዛቢ እስክናገኝ ስለማይጨው ጦርነት የነበረ የዓይን ምስክር አንድ በቅርቡ ያነበብሁት መጽሐፍ ትዝ አለኝ፤ አንድ የቼኮዝላቫኪያ ጎበዝ የጻፈውን የሃበሻ ጀብዱ የሚል መጽሐፍ ተጫነ ጆብሬ መኮንን የተባለ ሰው የተረጎመውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳትሞታል፤ አቶ ስብሓት ብቻ ሳይሆን ማንበብ የሚችል ሁሉ ሊያነብበው የሚገባ መጽሐፍ ነው፤ እኔ ፈረንጅ ስለኢትዮጵያ የፃፈውን ማንበብ ከተውሁ ብዙ ዓመታት ሆኖኛል፡፡ ይህንን ግን በአንድ ቀን ተኩል ጨረስሁት፤ የኢትዮጵያን ዘማቾች ከኋላ እያጠቁ ስለነበሩት “የትግራይ ሽፍቶች” ማን ይናገር? የነበረ፤ ነውና እንዲህ ይላል፡-
“ የትግራይ ሽፍቶች ለምን ወንድሞቻቸውን ይገድላሉ?… ከመሀል አገር ስድስትና ሰባት ወር ሙሉ ፍዳውን እያየ ሲጓዝ ከርሞ እዚህ የደረሰው ወንድማቸው፣ የነዚህን ምስኪኖች ህይወትና ንብረት ከጠላት ለመከላከል የገዛ ህይወቱን አልጋ ላይ ጥሎ፣ ቤት ንብረቱን በትኖ መከራውን ባየ ለምን ይገድሉታል?”
እነዚህ ሽፍቶች ወንድሙን የገደሉበት አብቹ የሚባል የአስራ ስድስት ዓመት የሰላሌ ዘማች በጣም ተናዶ የራሱን የግል ቡድን አቋቁሞ ያሳድዳቸው ነበር፡፡

ኢትዮ ሪፈረንስ:- የሃበሻ ጀብዱን ሁሉም ኢትዮጵያዊ  እንዲያነበው እንመክራለን!

ከመጽሃፉ ጀርባ የተቀመጠው

የቼኩ ሪፐብሊኩ ተወላጂ የዚህ መጽሃፍ ደራሲ ኣዶስፍ ፕርለሳክ- ትርጉም ተጫነ ጆብሬ መኮንንየቼኩ ሪፐብሊኩ ተወላጅ የዚህ መጽሃፍ ደራሲ ኣዶልፍ ፕርለሳክ ቀደም ሲል ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙ ሃገሮችን የጎበኙ ሲሆን፣ በ1935 እ.ኤ.ኣ. ወደ ኢትዮጵያ ተመስለው በመምጣት ከንጉሰ ነገስቱ ፊት ቀርበው የኢትዮጵያን መኮንንነት ማዕረግ ከተሾሙ በኃላ የሰሜኑ ጦር ጠቅላይ ኣዛዥ ለነበሩት ራስ ካሳ ኃይሉ የጦር ኣማካሪ በመሆን ኣገልግለዋል። በዚሁ ወቅት በመቶ ሺዎች ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ጎን ሆነው ታግለዋል። መጽሃፉ ሃበሽስካ ኦዴሳ (HABESSKA ODYSSEA) – የሃበሻ ጀብዱ፣ የዚያን የገበሬ ጦር ጀግንነት ለመዘከር የጻፉት ነው። ኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ

 

 

Filed in: Amharic