>

ሀብታሙ አያሌው በኩላሊት ጠጠር ታመመ [ኤሊያስ ገብሩ]

Habtamu Ayalew Andinetየቀድሞ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረው ሀብታሙ አያሌው፣ በኩላሊት ጠጠር መታመሙ ታውቋል፡፡ በዛሬው ዕለት ዘውዲቱ ሆስፒታል ለህክምና መምጣጡ የተረጋገጠ ሲሆን፣ የህክምና ምርመራ ያደረገለት ዶ/ርም፤ ሀብታሙ በሁለቱም ጎኑ በኩላሊት በጠጠር ችግር ሳቢያ መታመሙን እንደገለጸላት ባለቤቱ ወ/ሮ ቤተልሄም ተናግራለች፡፡ ሀብታሙም ላጋጠመው ህመም ምርመራ ተደርጎለት እና መድሃኒት ተሰጥቶት በአሁኑ ሰዓት ወደቂሊንጦ እስር ቤት ሊመለስ መኪና እየጠበቀ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Filed in: Amharic