>

ተሰፋ የቆረጡ ሰደተኞችን “የደበደበች’ ጋዜጠኛ ከሰራዋ ተባረረች [ታምሩ ገዳ]

by Tamru Gedaከርስ በርስ ጦርነት እና ከ አክራሪው የ አይ ኤስ ጥቃቶች ሸሽተው በምእራብ አውሮፓ ወስጥ ለመጠለል ሰሞኑን እንደጎርፍ የሚተሙት እና ተሰፋ ሰንቀው ቢጓዙም የተለያዩ በደሎች የገጠሟቸው የመካከለኛው ምስራቅ እና የአፍሪካ ሰደተኞች ሁናቴን በቴሊቭዥን መሰኮት ለተመለከተ ልቡ የማይነካ ሰብ አዊ ፈጡር ያለ አይመሰልም።

በተለይ ደግሞ ይህንን የዘመናችን ታላቅ የሰበአዊ ቀውስ እና ሰቆቃን ከሰፈራው ደረስ በመገኘት በምስል እና በደምጽ ቀረጸው ለተመልካቾች ፣ለአድማጮች እና ለአንባቢዊያን የሚያደረሱ ጋዜጠኞች ሃላፊነታቸው እና ሃዘናቸው ድርብ ድርብርብ ነው።ታዲያ በምስራቅ አውሮፓዊቷ ( በሃንጋሪይ) በኩል ወደ ምእረብ አውሮፓዎቹ እነ ጀርመን፣እንግሊዝ ፣ስዊድን የመሳሰሉት አገሮች ለመሸጋገር በደንበር ላይ የተኮለኮሉት በመቶዎች የሚገመቱ ተሰፋ የቆረጡ የሶሪያ ሰደተኞች ባለፈው ማክሰኞ ከሃንጋሪ ፖሊሶች ጋር በተፋጠጡበት ወቅት ሁኔታውን ለመዘገብ በርካታ አለም አቀፍ ጋዜጠኞች በሰፈራው ተገኝተው ነበር።

ይሁን እና ለሃንጋሪው በሄርተኛ እና ጸረ ሰደተኞች ለሆነው ቴለቪዥን( N1 TV ) ጋዜጠኛ እና ምስል ቀራጭ የሆነችው ፔትራ ላሳዛሎ አንድ ከሶሪያው ጦርነት ያመለጡ ዳግም ከሃንጋሪ ፖሊሶች ጋር የተጋፈጡ አባት ጨቅላ ልጃቸውን ታቅፈው ከፖሊሶቹ በመሸሽ ላይ ሳሉ የመቅረጫ ካሜራውን በምስኪኑ ስደተኛ ላይ ያነጣጠረች ጋዜጠኛ ተብዮዋ ፔትራ እግሯን (እንደ ካራቲስት) በመሰንዘር በሽሽት ላይ የነበሩ ሶርያዊው አባትን በመጥለፍ ሰደተኛው አባትም በጨቅላው እና በብርቅዩው ልጃቸው ላይ በመውደቃቸው ልጃቸው ምርር ብሎ ሲያለቅሰ እርሻቸውም ሲራገሙ ጋዜጠኛ ተብዩዋ ካሜራዋን ወድራ መቅረጿን አላቆመችም ነበር ።ከዚያም በሁዋላ ከፖሊስ ከበባ እና ወከባ ለማምለጥ የሞከሩ ሌላ አንዲት ልጃገርድ እና አንድ ጨቅላ ህጻንን በጠረባ በመምታት መጣሉዋን በምስል የተደገፉ ማሰረጅዎች አጋልጠዋታል።ግለሰቧ ቀደም ሲልም በርካታ የሶሪያ ሰደተኞችን ሳትደበደብ እና በእግሯ ሳትጠልፍ እንዳልቀረች ተገምቷል።

ይህንን 20 ሰኮንዶች የፈጀው ነገር ግን አሳዛኝ እና ሞራላዊነት የጎደለው ትውኔትን የጀርመኑ RTL ቴሌቭዥን ጋዜጠኛ ስቲፋን ሪቸር ምስሉን በቲዊተር አካውንቱ ላይ መለጠፉን ተከትሎ ደርጊቱ በመላው አለም በመሰራጨቱ የተገፉ ወገኖች አይን እና ጆሮ መሆን የነበረባት ነገር ግን በተቃራኔው በመቆም ፍጹም ሰበዊነት እና እርህራሄ የጎደላት ፔትራ ከተቀጠረቸበት የቴሊቭዥን ጣቢያ ጋር የነበራት የስራ ኮንትራትም ያለ ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ (በቅጽበት) ተቋርጧል ። ቀጣሪዋ ጣቢያም “አሳፋሪ እና ተቀባይነት የጎደለው ምግባር “ በማለት የውግዘት መግለጫ ወዲያውኑ አውጥቷል ። በርካታ ወገኖች ነዴታቸውን በግለሰቧ ላይ ያሰሙ ሲሆን በኣንድ ቀን ውስጥ ብቻ ከ 16ሺህ በላይ የፊስ ቡክ ተጠቃሚዎች “የማፈሪያ ግድግዳ “በሚል አዲስ አካዋንት ላይ በገለሰቧ ላይ የተሰማቸውን ቅሬታቸወን አስፍረዋል። ፔትራም ይህንን እኩይ ተግባር ለመፈጸም ምን እንደገፋፋት ኣስከ አሁን ድረስ አስተያየት አለሰጠችም። የአገሪቱም አቃቢ ህግም ግለሰቧን እንዴት እንደሚከሰስ ጉዳዩን “ሃሙስ እለት እያጠናው መሆኑን ይፋ አድርጓል።ጋከአገሪቱ ፖሊሶች በላይ የሰብአዊ መብት ረጋጭ ሆና የተገኘችው ጋዜጠኛ ተበዩዋ ጥፋተኛ ሆና ከተገኘች ሰዎች ላይ አካላዊ ጥቃት በመሰንዘር ወንጀል እስከ 5 አመት ወደ ኣስር ቤት ልትወረወር ትችላለች። የቀበጡ እለት ,,,, ይሉሃል ይሄኔ ነው።https://youtu.be/pVtBfSgAub0

Filed in: Amharic