”የኣቶ ኣንዳርጋቸው 60ኛው ዓመት የልደት በዓል ላይ በመገኘቴ ደስተኝ ነኝ”
”ኣቶ ኣንዳርጋቸው ጽጌን መስከረም 28/2013 በኖርዌይ – ኦስሎ ባደረጉት ዝግጅት ላይ ለመካፈል እድሉን ኣግኝቼ ነበር። ያን ጊዜም ዝግጅቱን ለመታደም የመጣሁት ከስታቫንገር ነበር። ያን ጊዜ እሳቸውን በቅርብ ለማወቅ ዕድሉን ኣግኝቻለሁ ማለት እችላለሁ። ለኢትዮጵያ ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር ኣስተውያለሁ። የሰላሙ በር እስኪዘጋባቸው ድረስ የቻሉትን ሁሉ የሞከሩ ሰው ናቸው።ኣቶ ኣንዳርጋቸው ጽጌ ወያኔ/ኢህኣዲግን በሁሉም ነገር ኣሸንፈውታል። እኛን ሁሉ ያፈሩት ኣቶ ኣንዳርጋቸው ጽጌ ናቸው። ዛሬ ሁላችንም ኣንዳርጋቸው ጽጌ ነን።
60ኛው የልደት በዓላቸውን ሁሉም ነገር ተለውጦ ኣንዳርጋቸው የሚመኙዋት ኢትዮጵያን ኣይተን የምናከብረው ልደት ቢሆን ደስታዬ ይበልጥ ነበር። ኣሁንም ለዚያ የሚያስፈልገውን ጠጠር ሁላችንም በኣቅማችን መወርወር ከቻልን ኣንዳርጋቸው ጽጌ የዘረጋልን የትግል መንፈስና በጣለልን መሰረት መጨረሻው መድረሱ የማይቀር መሆኑን እረዳለሁ።” በማለት የገለጸችልን ትዕግስት ታደሰ ስትሆን፣ ኣቶ ዓለሙ ኣዱኛ ፈረደም በበኩላቸው:- ኦስሎ በዝግጅቱ ላይ ለመገኘት ትራንስፖርት ቲኬት ኣጥተው በውድ እንደገዙ ነግረውን፤ በኣቶ ኣንዳርጋቸው መታሰቢያ ዕለት መገኘታቸውን የገለጹልን እንዲህ በማለት ነበር።
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ኖርዌይ ኦስሎ በ”ኣንቲ-ራሲስት ሴንተር” በተያዘው ኣዳራሽ ውስጥ ከኖርዌይ ከተለያዩ ከተሞች ስታቫንገር፣ በርገን፣ ኦስሎና ኣካባቢዋ የሚገኙ የድርጅቱ ኣባላቶችና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያኖች በተገኙበት በተያዘለት መርሃ ግብር መሰረት የኣቶ ኣንዳርጋቸው ጽጌ 60ኛ ዓመት የልደት በዓል በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።(ኢትዮ- ሪፈረንስ)