ይህንንም ለማረጋገጥ ለኢትዮጵያ አገራችን ነጻነትና ፍትህ ለማስፈን የህይወት መስዋትነትን እስከ መክፈል ድረስ እየታገለ የሚገኘውን የነጻነት ተምሳሌት የጀግናው አንዳርጋቸው ጽጌ ፷ኛ ዓመት የልደት በዓልን በዓለም አቀፍ ደረጃ በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በዝግጅት ላይ እንገኛለን።
ስለዚህ ዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ በወጣቶች ክፍል አዘጋጅነት በኖርዌይ ለምትኖሩ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በልደት በዓሉ ላይ ተገኝታችሁ ለአንዳርጋቸው የአላችሁን አክብሮት ትገልጹ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
በዝግጅቱም ላይ
- የአርበኛው አንዳርጋቸው ጽጌ ለኢትዮጵያ ነጻነት ያደረገው አስትዋጾ በዝርዝር
- የትግል ዓላማውና ለኢትዮጵያ ያለው ራእይ
- ሥነጽሁፎችና ስሜት ቀስቃሽ አገራዊ የኪነ ጥበብ ዜማዎች እና ሌሎችም ይቀርባሉ
ቀን፡ ፌብሯሪ 14/2015 ከ16፡00_ 22፡00 ስዓት
የዝግጅት ቦታ: Antirasistisk Center, Storgaten 25
የአንዳርጋቸውን ራእይ እውን እናደርጋለን!
ወያኔን ከህዝባችን ጫንቃ ላይ እናወርዳለን!
የኢትዮጵያን የክብር ትንሳኤ እናያለን!
ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
የዲሴሶን ወጣቶች ክፍል