>

ግንቦት ሰባት ከልምድህ… (ግርማ በላይ)


ግንቦት ሰባት ከልምድህ…

ግርማ በላይ

አጤ ምኒልል ከልምድዎ፤
አንዳንድ እያለ ቀረልዎ፤
አምናስ አለማያ ነበሩ፤
ዘንድሮን ወዴት ዋሉ?

ግንቦት ሰባት ከልምድህ፤
አንዳንድ እያለ ቀረልህ፤
አምናስ አሥመራ ነበርክ፤
ዘንድሮን ወዴት ዋልክ?

የኢትዮጵያ ሾተላይ ግዳይ መጣሉን ቀጥሏል፡፡ ልጆቿን ለሆነ ዓላማ ያሰባስባል፤ ከዚያም ቁም ነገር ሊያከናውኑ ሲሉ አንዳች ነገር ብን ያደርግባቸውና እያባላ ይበትናቸዋል – ደብተራዎች “አንደርብ” እንደሚሉት ዓይነት ነገር፡፡ ሀገሪቱ የሰብስብ ሣይሆን የበትን አለባት፡፡ ኢትዮጵያ ከምትወልዳቸው ልጆቿ ሙሉ በሙሉ ሳታያቸው በባህሉ መሠረት የጥቂቶቻችንን ጆሮ ቀንጠብ አድርገው ሰጥተዋት ካልበላችና የልጇን ጆሮ መብላቷን ነግረው ካላስደነገጧት በስተቀር የሾተላይ ዛሯ እንደ ሀገር የመቀጠሏን ዕድል እያጫጫው ነው፡፡ አሁንማ ሁሉ ነገር ኳስ አበደች ሆኗል፡፡ መንግሥት የለ፤ ሕዝብ የለ፡፡ ኦና ብቻ! ኦና ሀገር፡፡ ንብ-አልባ ቀፎ ሆነናል፡፡

ነዓምን ዘለቀ ከግንቦት ሰባት መውጣቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው፡፡ እዚህ ደረጃ እስኪደርስ ብዙ ነገሮችን ተቋቁሞና ራሱን እየጎዳ መሆን አለበት፡፡ እንጂ በአንዴ ይህን መሰል ውሳኔ ላይ አይደርስም፡፡ እኛ ታዛቢዎችም እንል የነበረው ከዚህ የተለዬ አልነበረም፡፡ ደግሞም በምክንያትነት ከተናገረው ይልቅ ያልተናገረው እንደሚበልጥ መገመት ይቻላል፡፡ “ግንቦት ሰባትን ያመነ ጉም የዘገነ” ይሏል እንግዲህ አሁን ነው፡፡ አዎ፣ የዚያ ሸፍጠኛ ትውልድ ውጤት እንደዚህ ነው፡፡ ለራሱም ለሀገርም አይሆንም፡፡ መልቲ ሁልጊዜም መልቲ ነው፡፡ መቅጠፍጠፍ እንጂ ቁም ነገር የለውም፡፡ ለታይታና ለይምሰል ዲሞክራሲ ይላል – በተግባር ግን አያውቀውም፡፡ ግንቦት ሰባት ስንትና ስንት አካይስት ተግባር እንደፈጸመ ለመረዳት መዛግብትን መፈተሸ ነው፡፡ የመጥፎ ድርጊት ባለቤቶች ግን የሚሠሩትን ግፍ እንደጽድቅ ይቆጥራሉ እንጂ ለንስሃ የተፈጠሩ አይደሉምና ዕኩይ ሥ(ሤ)ራቸውን አያምኑም፡፡ ከዚያም ባለፈ ሰውን በመወንጀልና በመሳደብ የሚስተካከላቸው የለም፡፡ “ሞኝ እንዴት ያሸንፋል?” ቢሉ “እምቢ ብሎ” እንደሚባለው ይሄውና ለምሣሌ ከነሱ ጋር በሌለ – “አጉራችሁ ጠናኝ” ብሎ በተለያቸው ድርጅት እስካሁን እየተጠሩበት ነው፡፡ ይህን ምን ትሉታላችሁ? “ካፈርኩ አይመልሰኝ” ድርቅና ወይንስ የዕውቀት ብዛት አናፍሏቸው? መቼውንም የማይገባኝ ነገር ነው ይሄ፡፡

አባባሉ አስቀምጦታል፡፡ “ሽልም ከሆነ ይገፋል፤ ቂጣም ከሆነ ይጠፋል፡፡” በአሁኑ ወቅት ብዙ ቂጣዎች ጠፍተው ሽሎች ሊወለዱ እየተንቆረዘዙ ናቸው፡፡ ይወለዳሉ፡፡ ጀግኖች አዋላጆችም በየድብቅ ሥፍራዎች እየተዘጋጁ ነው – ለሚታየው ይታየዋል፡፡ በዱባ ጥጋብ የደነዘዙና ይሠሩትን ያጡ ነብራራዎችም በሚያደርጉት ነውረኛ ተግባር በደስታ ጮቤ እየረገጡ ግፋቸውን ይቀጥሉ፡፡ ቤት ለማፍረስ የተሾሙ የአይሲስና የአልቃኢዳ ፍልስፍና አራማጅ የሆነው ኦነጋዊ ኦህዲድም በግላጭ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ማሳደዱን ይቀጥል፡፡ ያለችው ጊዜ አጭር ናትና መሳነፍ የለበትም፡፡ የሚያቃጥለውንም ሆነ የሚሸጥ የሚለውጠውን በቶሎ ያከናውን፡፡ጊዜ የለውም፡፡ “ወያኔ አባት ሳለ አጊጥ፤ ፀሐይ ሳለ ሩጥ” ነው ነገሩ፡፡
ባልተቤቷን ያናደደች መስሏት ገላዋን በሹል እንጨት የቦጫጨረችውን ሞኟን ሚስት የሚመስለውን ሕወሓትንም ግፋ በሉት፡፡ ጊዜው አሁንም የነርሱ ነው – የሕወሓቶች፡፡ ሞኝ አሽከርን በቀጭኑ ሽቦ እያዘዙ አገርን ማቃጠል ለጊዜው ደስ ይላል – ለሀዘን አምላኪዎች፡፡ “ገንዘብ የተሸከመች አህያ የማትደረማምሰው ምሽግ የለም”ና የፈለጉትን ሁሉ አሁኑኑ ይደረማምሱ፡፡ ከዋሻቸው ውስጥ ሆነው ጃዝ የሚሉትን ጀዝባ ቡድን ተክተው በመሄዳቸው ለተወሰነ ጊዜ እነሱም በደስታ ይቦርቁ፡፡

ወያኔ አዲስ አበባን በከፍተኛ ደረጃ ተቆጣጥሮ በነገድ አባላቱ ኢኮኖሚውን እየቦጠቦጠ ባለበት በአሁኑ ወቅት ጀለንፎዎቹ ኦነግና ኦህዲድ አማራ ላይ የሙጥኝ ብለዋል – “ሞኝና ወረቀት የያዘውን አይለቅ” ነውና ለ40 ምናምን ዓመታት ወያኔ ስትግታቸው የነበረውን ፕሮፓጋንዳ ይዘው እየተጃጃሉ ይገኛሉ – ይቅናቸው፤ ግን ነፍስያቸው በማትፈቅደው መንገድ በጥፋት ጎዳና እየተመሙ በመሆናቸው እነሱም ከልብ ያሳዝኑኛል፡፡ እነዚህ ከኦሮሞ ሰውነት እጅግ ባነሰ ሁኔታ የተሰፉ አሣፋሪ ልጆች የሚያደርጉት ሁሉ በነገው ታሪካችን ምን ያህል አሣፋሪ እንደሆነ ከአሁኑ ልንመሰክር የግድ ነው፡፡ አማራንና ጉራጌን ከመሀል አዲስ አበባ አውጥቶ በዳርና ዳር ያስቀመጠው ሕወሓትና ጀሌዎቹ “ፊንፊኔ”ን ተቆጣጥረው እያለ ያሸነፉ የመሰላቸው አማራን አላስቆም አላስቀምጥ ብለዋል – ተደጋግማ በመተረቷ ምክንያት አንባዎቼን ታሰለችብኛለች ብዬ እንጂ ያቺን “የምታሸንፈውን ምታ ቢሉት ወደሚስቱ ሮጠ” የምትባል ተረት መተረት አምሮኝ ነበር፡፡ ሰሞነኛው ጉዳችን ታሪክን በቅርብ ርቀት የደገመ የሚገርም አካሄድ ነው፡፡ ይህ ለማንም የማያዋጣ ሥልታዊ ወዳጅነት ደግሞ በቂልነትና በማይምነት የተሞላ መሆኑ በግልጽ ይታያል፡፡ “ማንም ለማይጠቀምበት ዕልቂት ይልቁንስ ሕዝቡን በከንቱ ለማስፈጀት አትቋምጡ” በማለት ወዳጆቻቸው ይምከሯቸው፡፡ ኦነግ የ84ቱን ቂም ረስቶ ከወያኔ ጋር ተባብሮ አማራን ካጠቃ በኋላ ትግሬን በመሀል አገር ያኖራል ብሎ ማሰብ የመጨረሻ ቂልነት ነው፡፡ ብዙ ድንቁርና ይታየኛል፡፡ ጤነኛ ኦሮሞዎች፣ ጤነኛ አማሮች፣ ጤነኛ ትግሬዎች…. ተነሱና ይህን የማይማንና የሾለክላካ እባቦች ወጥመድና መርዝ አርክሱ፡፡ ነግሬያለሁ!

ስማኝማ፡፡ እሳትና ውኃ ጥቅሙም ሆነ ጉዳቱ ዘርን አይለይም፡፡ መቀሌ ላይ መሽገህ ጃዝ የምትል ወሮበላም ሆንክ እዚህ አዲስ አበባ ማለቴ ይቅርታ ፊንፊኔ ላይ ቀን ሰጠኝ ብለህ የምትደነፋ ጅላጅል ሁላ እዚህ ከተማም ሆነ እዚህች ሀገር የሚፈነዳ ጦርነት አማራን ብቻ እየለዬ የሚገድል፣ ኦሮሞና ትግሬን እየመረጠ የሚተው ከመሰለህ በርግጥም በግ ነህ፡፡ የጎርፍ ውኃ አይምጣ እንጂ ከመጣ ማንንም አይመርጥም፤ አይምርምም፡፡ አንድ አካባቢ የሚነሳ እሳት አይነሳ እንጂ ማንንም አይመርጥም፤ አይምርም፡፡ መቀሌ የመሸግህ ወያኔ አንተ ብታመልጥ ባንተ ጦስ በመላዋ ኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ ሀብት ንብረት አፍርቶ ተደላድሎ የሚኖረው ትግሬ ከአማራ ወገኑ ጋር ተደርቦ ማለቁ የማይቀር ነው፡፡ የጥይት መተኮሻ ማነጣጠሪያዎች ዒላማቸው ሰው ይሁን እንጂ ማንንም ከማንም አይለዩም – ግንባሩ ላይ መስቀል ያለውን ወይም “ዱቤ ክልክል ነው” የሚል ንቅሣት ያለውን፣ 11 ቁጥር ያለውን፣ የሣንቲም ቅርጽ ያለውን ወዘተ. ለመግደል ወይ ለመተው ጠበንጃዊ ፎርሙላ አልተሠራም፡፡ ምሽግ ደርማሽ የጦር መሣሪያዎች የትግሬን ሕንጻ ከኦሮሞ ሕንፃ የሚለዩበት ረቂቅ መንፈሣዊ ዐይን የላቸውም፡፡ ብዙ የሞኝነት አካሄድ እየታዘብኩ ነው፡፡ ሰው በጤናው እንዴት ሦርያንና ሶማሊያን ይመኛል? እነዚህ ትግሬና ኦሮሞ ነን ባይ አሰለጦች የያዙት የፍጅት መንገድ በቅጡ ያልታሰበበት በመሆኑ ማንን ከማን ለይተው ሊጠቅሙ ወይ ሊጎዱ እንደፈለጉ ራሱ አልገባህ ብሎኝ እየደነቀኝ አለሁ፡፡ እንደሦርያ እንዳንሆን እያልን ስንጨቀጭቅ የፍርሀት መስሏቸው እነኦነግና ኦህዲድ በጉራና በትዕቢት ተወጥረው ሕዝባችን ነው የሚሉትን ሳይቀር ወደ እቶን ሊጨምሩት እንደጠገበ ኮርማ ሌት ከቀን በጦር አምጣ መሬትን እየፎከቱ ነው – ይመጣላቸዋል፡፡ እግዜር የለመኑትን አይነሣም፤ የነገሩትን አይረሣም፡፡ ዛሬ የምሥኪን ዜጎችን ቤትና ሀብት ንብረት ቢያፈርሱ እግዚአብሔር ምሥክሬ ነው በቅርቢ የሚገቡበትን ያጣሉ – ደግሞም የሚገርመው ሴት ሙስሊሞችን ነው ያሰማሩት – “ሴት ጨካኝ ናት” የሚለውን የቀደመ ግን “ኋላ ቀር” ብሂል በማስታወስ ይመስላል፡፡ (44 ሽህ ቤት ካላፈረስኩ ‹ጣቴ ይቆረጥ› አለች አሉ ያቺ የሱልልታዋ አህመድ ግራኚት?)የሚጠሩትን ዕልቂት ይበልጥ ማን እንደሚጋተውም እናይ ይሆናል፡፡ በርግጥ እነሱ እሳቱን ለኩሰው ወደ አንድ ጥጋት እንደሚሸሹና በትያትር መልክ የሕዝብን መፋጀት እንደሚመለከቱ እሙን ነው፡፡ ፈጣሪ ግን እንደዚያ አያደርገውም፡፡ የሚጭሯትን እሳት ሳይሞቋት አይቀሩም፡፡

በነገራችን ላይ ኦነግ-ኦህዲድ የጭፍጨፋ የሙከራ ሥርጭቱን በቦሌ ሚካኤል አካባቢ እንደጀመረና ጃዋራዊ ሜንጫውን እያሟሟቀ እንደሆነ በዛሬ ዘገባዎች እየተገነዘብን ነው – ያገሬ ሰው “ካልጠገቡ አይዘሉ፤ ካልዘለሉ አይሰበሩ” የሚለው ወዶ አይደለም፡፡ ይህ ሁሉ የጥጋብ ጉዞ ምን ሊያመጣባቸው እንደሚችል … ዘመድኩን በቀለ የምትባለው ልጅ እባህን አግዘኝና በዚህች ነጥብ ዙሪያ አንዳች ነገር በልልኝማ …. ፡፡ ለማንኛውም ዳግማዊ ወያኔዎች በኢትዮጵያ የውስጥና የውጭ ጠላቶች ምክርና ሁለንተናዊ እገዛ ተኩራርተው ለማይቀረው ፊንፊኔያዊ አርማጌዴዖን እየተዘሃጁ ነው – የመቶ ዓመቱ የቤት ሥራም ሊገባደድ የቀረው ጊዜ በጣም ጥቂት ነው – እናውቀዋለን እባክህን፡፡ በአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያ ተወጥራለች – ግን የመጨረሻውን መድኅን ልጇን በቅርብ ተገላግላ ነፃነቷን ትቀዳጃለች፡፡ እነ “ሱሴ” ግን መንገዱን ጨርቅ ያድርግላቸው፡፡ የቀጣፊ ቀን መጨረሻ ደርሷል፡፡

ግን ግን ኦህዲድ በጊዜ ጠባዩን ባያሳውቀን ኖሮ ምን ይውጠን ነበር? እንደወያኔ እያለሳለሰ ቢገዛ ኖሮ እኮ ብዙ እንቸገር ነበር፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ግን እግዜር ይስጣቸው ገና ሩብ ዓመትምሥልጣን ላይ ሳይደላደሉ በአማራና በሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ የጭቃ ጅራፋቸውን ማንጓት ጀመሩ፡፡ ጠላትን ቀድሞ ማወቅ ከብዙ አቅጣጫ ሲታይ ጠቃሚ ነው፡፡ አይጠቅምም እንዴ?

ልሣንን ለወጥ አድርጎ መራቀቅ አንዳንዴ መጥፎ አይደለም፡፡ It is really a blessing in disguise that OPDO has shown its intrinsic nature within the past few months. I guess this golden opportunity must have been allowed by His benign intervention for divine purpose. Now, it is up to sane Ethiopians to unite and put their efforts together to get rid of these historically good-for-nothing people altogether. All Ethiopians who claim to be genuine Ethiopians should take note of the Amharic saying, “በጊዜ የጮኸ ጅብ አያሳድረኝም”. We should use this incidence to discern the grain from the chaff; the goodie from the riffraff; the real Ethiopians, whose fate has been similar, from the pseudo or fake ones. Thanks to the leeside of flowery words of shrewd “Ethiopians” who ‘vowed’ to stand for the rights of all Ethiopians irrespective of their ethnicity, religion, language etc., for they made us rethink of the susceptibility of the Ethiopian politics. Thanks to these “levelheaded” leaders of the Oromized revolution who helped our tears knock at the doors of the heavens. Thanks to the pugnacious nature of our revolutionaries who are by now acting like a mad dog and quarreling almost with all ethnics, perhaps, except with Tigrians, due to the alleged strategic alliance, of course. Thanks to their lunatic behavior that has made the rest of us get united for a common goal of rebuilding our nation. But take care of the upcoming tidal weather.…

Filed in: Amharic