>
5:13 pm - Wednesday April 20, 3104

በዶ/ር አቢይ መንግስት በመታየት ላይ ያሉ ሃገራዊ ለውጦችና ቀሪ የቤት ስራዎች !!! (አባተ ደግአረገ)

በዶ/ር አቢይ መንግስት በመታየት ላይ ያሉ ሃገራዊ ለውጦችና ቀሪ የቤት ስራዎች !!!
አባተ ደግአረገ
ምንም እንኳ ሙሉ በሙሉም ባይባል የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች ቀስ በቀስ  እየተቀረፉ ይመስላል ።
  ህዝባዊ እምቢተኝነቱ አሼንፎ የለውጥ ኃይላትን ወደ ስልጣን ካመጣ ወዲህ የዶ/ር አቢይ መንግስት የሚከተሉትን ችግሮች ሙሉ በሙሉ አሊያም በአብዛኛው ቀርፏል  ብየ አምናለሁ ።
 
1ኛ)  ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመደመሪያ ጊዜ ጋዜጠኞች እስር ቤት ውስጥ የማይገኝባት ሃገር እንድትሆን ተደርጓል ።
 
2ኛ) ተዘግተው የነበሩ ድህረ ገፆች ዜጎች በነፃነት እንዲነብቡ ተደርጓል ።
 
3ኛ) ዜጎች በነፃነት የፈለጉትን ሃሳብ በሰላማዊ ሰልፍና በጽሁፍ እንዲገልጹ ተደርጓል ።
 
4ኛ) የመከላከያ ሰራዊቱና የመንግስት ተቋማት  የአንድ ዘር መገልገያ ከመሆን እንዲፀዱ ተደርጓል ።
 
5ኛ) ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላት ተሰሚነት  እንዲጨምር ተደርጓል ።
 
  6ኛ) ኤምባሲዎች የአንድ ዘር መፈንጫ ከመሆን ፀድተው  የህዝብ መገልገያ እንዲሆኑ ተደርጓል ።
 
7ኛ) በአንድ ክልል ሌቦች  ተይዞ  የቆዩ የመንግስት መገናኛ ብዙኃን የህዝብ ልሳን እንዲሆኑ የማስተካከያ ስራ ተሰርቷል ። 
 
8ኛ) የህወኃት አከርካሬ ተሰብሮአል ።  ህወኃት ጨርሶ አልጠፋም ግን እጅና እግሮቹ ተሰባብረው ምላሱ ብቻ ቀርቷል ። 
 
9ኛ) ሃገርን የዘረፉ ሌቦችና ወንጄል የሰሩ ባለ ስልጣናትን ወደ ፍትህ የማምጣቱ ስራ በከፊል ተጄምሯል ።
 
10ኛ) በውጭ የሚገኙ ዜጎች በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሃገር እንደፈለጉ እንዲገቡና እንዲወጡ ተደርጓል ።
 
11ኛ) የምርጫ ሂደቱን ለሁሉም ተፎካካሪ ኃይሎች ምቹ ለማድረግ እርምጃ በመወሰድ ላይ ነው ።
 
12ኛ) የማህበረሰቡ ግማሽ አካል የሆኑት ሴቶች የቢሮ ስራዎችን እንዲሰሩ ሹመት ተሰጥቷቸዋል ።
 
13ኛ) የፍትህ ስርዓቱ ላይ ማስተካከያ በማድረግ ፍ/ቤቶችን በአዲስ መልክ የማዋቀር ስራ ተሰርቷል ።
 
14ኛ) ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ተፈትተዋል ።
 
15ኛ) አንዳንድ የመንግስት የንግድ  ሴክተሮች ወደ ግል እንዲዘዋወሩ ተደርጓል ።
 
16ኛ) ለዘመናት የታፈኑ የዲያስፖራ ድምጾች በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲደመጡ ተደርጓል ።  
 
 17ኛ) እንደ አብዲ ኢሌ አይነት ፀረ ህዝብ አመራሮች ከስልጣን ወርደው  ወደ ህግ እንዲቀርቡ ተደርጓል ።
 
18ኛ)  በሙስና ላይ መጠነ ሰፊ ጦርነትነ  እንዲከፈት ተደርጓል ።
 
19ኛ)  በባዕድ ሃገር በተለይም በግብጽ ፣ በሱዳንና በሳኡዲ የታሰሩ ዜጎች እንዲለቀቁ ተደርጓል ።
 
20ኛ) ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች በነፃ እንዲንቀሳቀሱ ተደርጓል ።
 
ቀሪ የቤት ስራዎች ….
 
21ኛ)  ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ያልተያዙ ወንጀለኞች በህግ ቁጥጥር ስር ሊውሉ ይገባል ። 
 
22ኛ) በሌቦች ተመዝብሮ በውጭ የተቀመጠ የህዝብ ንብረት ወደ ሃገር እንዲመለስ መደረግ ይኖርበታል ።
 
23ኛ) የህወኃት ድርጅት በሃገር አቀፍ ደረጃና ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ እንደ ናዚ ፓርቲ በሽብር መዝገብ እንዲሰፍርና እንዲታገድ  ሊደረግ ይገባል ።
 
24ኛ) ነፃ ታማአኒና ፍትህአዊ ምርጫ በአስቸኳይ ሊደረግ ይገባል ።
 
25ኛ) በውጭ የሚኖረው ዲያስፖራ ጣምራ ዜግነት እንዲያገኝና በሃገሩ ሃብት ንብረቱን  እንደፈለገ እንዲያንቀሳቅስ ሊፈቀድለት ይገባል ።
 
26ኛ) ህዝብን የሚያፈናቅሉ ሁሉ በአስቸኳይ ተይዘው ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ ይገባል ።
 
27ኛ)  የኢንጅነር ስመኘው እውነተኛ ገዳዮችን በማፈላለግ ለህግ ማቅረብ ይገባል ።
 
28ኛ) የኤፈርት ንብረት የኢትዮጵያ ህዝብ ንብረት በመሆኑ ወደ ኢትዮጵያ ካዝና ሊገባ ይገባል።
 
  ስለ ለውጡ የዶ/ር አቢይን መንግስት እናመሰግናለን ።
Filed in: Amharic