ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
በዘ ሚካኤል ጆርጅ
☞“የኢትዮጵያ ህዝብ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የፍትህ ጥያቄ ሲያቀርብ ነበር” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፥ መንግስትም የህዝብ ጥያቄ መመለስ ውዴታው ብቻ ሳይሆን ግዴታውም እንደሆነ ገልፀዋል።
–
☞በአንድ ሀገር ውስጥ የመንግስት መኖርን የግዴታ ከሚያደርጉት መሰረታዊ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ፍትህን ማረጋገጥ እንደሆነም ገልፀዋል።
–
☞ፍትህ የሚረጋገጠውም ንጹሃን በኩራት ቀና ብለው የሚሄዱበትና ወንጀለኞች ደግሞ የትም የማይደበቁበት ስርዓት መፍጠር ስንችል ነው ሲሉም አስታውቀዋል።
–
☞ኢትዮጵያ ንፁሃን ዜጎች እንጂ ወንጀለኞች በኩራት የሚኖሩባት ሀገር መሆን የለባትም፡፡
–
☞ወንጀል ለፈፃሚው መጀመሪያ ጥቅም ያስገኘለት ቢመስለውም እየቆየ ግን ራሱን እየበላ ሄዶ መሸከም ከማይችልበት ደረጃ ላይ ይደርሳል ብለዋል።
–
☞አራዊት እንኳን የማይፈፅሙትን ኢሰብዓዊ ድርጊት በሰው ዘር ላይ የሚፈፅም ሰው በምን አንጀቱ ለወገኑ ይራራል፣ በየትኛው ልቡ ለወገኑ ያስባል በየትኛውስ አእምሮ ለወገኑ ይቆረቆራል ሲሉ የጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፥
☞ወንጀለኛ ማሰቢያው ጥቅም ብቻ ነው፤ ጥቅም ካገኘ ይዘርፋል፤ ያጠፋል፤ ይገላል፤ ያሰቃያል ያወድማል በማለት ነው ያብራሩት።
–
☞አሁን የተጀመረው ስራ ሀገር የገደሉ ወንጀለኞችን እነርሱ ለሌላው በነፈጉት ፍትህ ፊት የማቅረብ ስራ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የተያዙ ሰዎችም በተገቢ ደረጃና አያያዝ የሚገባቸውን ፍትህ እንዲያገኙ ይደረጋልም ብሏል፡፡
☞እያንዳንዱ ማህበረሰብ የተሸሸጉትን ወንጀለኞች አጋልጦ ለህግ በማስረከብ ወንጀል የሚያሳፍር መሆኑን እያሳየ መሆኑን ጠቅሰው፥ የህዝቡ ትብብርም እንደሚቀጥል ተስፋቸውን ገልፀዋል፡፡
☞የወንጀለኞች መኖሪያ መሆን ያለባቸው ማረሚያ ቤቶች እንጂ ብሄሮች ብሄረሰቦች አይደሉም ብለዋል፡፡
☞በመጨረሻም የቅጣቱ ዋና ዓላማ አጥፊዎችን መቅጣትና ድርጊቱን መኮነን ብቻ ሳይሆን ዳግም እንዳይከሰት መከላከልም ጭምር ነው ብለዋል በመግለጫቸው፡፡