>

ፖሊስ "ኢ/ር ስመኘው እራሱን አጠፋ" እያለን ነው?!? (ስንታየሁ ሀይሉ)

ፖሊስ “ኢ/ር ስመኘው እራሱን አጠፋ” እያለን ነው?!?
ስንታየሁ ሀይሉ
ዛሬም በተድበሰበሰ ምርመራ እና በተርበተበተ አንደበት ስለኢንጅነሩ አሟሟት እርስበርሱ የተጣረሰ እና በምርመራ ተቋም ደረጃ ወጥ ያልሆነና ተዓማኒነት የጎደለው የምርመራ ውጤት ላይ ኢንጅነሩ ራሳቸውን እንዳጠፉ በድፍረት ተገልፇል።
 በግሌ የኢ/ር ስመኘው ራስን የማጥፋት ተግባርን ለመቀበል ቢከብደኝም ከዚያ ተያይዞ ያሉት ምርመራዎች ሁሉ አሳፋሪ እና የተቀነባበረ ውሸት እንደሆነ መግለጫው ያሳብቃል።
– ኢ/ር ስመኘው ከመሞቱ በፊት የበተነው እና በመኪናው ውስጥ የተገኘው የፖስታ መልዕክት ይፋ አለመደረጉ ወይም “ለመሞት ያደረሰው ምክንያት አልተገለፀም ” ተብሎ መነገሩ በትልቅ ውሸት ትልቅ መረጃ መደበቁ ግልፅ ነው።
– ኢ/ር ስመኘው ከመሞቱ ሁለት ቀናት በፊት በቢቢሲ በሠጠው ቃለመጠይቅ በመልካም ሁኔታ ግንባታው እየተካሄደ እንደሆነ ተናግሮ እያለ በውስን ቀናት ውስጥ ራስን እስከማጥፋት የሚያደርስ መረበሽ አያደርሰውም።
– ኢ/ር ስመኘው ከሜቴክ ጋር ባለው ጫና እንዳይሆን የሜቴክ ዝርፊያ የአደባባይ ወሬ እና የሌሎች ተቋራጮች፣ የኤሌክትሪክ ኃይልና በመዝገብ ደረጃ ሁሉም የሚያውቁት እንደመሆኑ ለኢ/ሩ ራስን ማጥፋት የግል ድርሻም ሆነ ምክንያት አይሆንም።
– ኢ/ር ስመኘው በተገደለበት እለት ለጋዜጣዊ መግለጫ በቢሮው እንግዶች እንደተጋበዙ ተገልፆ በዛሬው እለት ደግሞ እንደ ጦስ ዶሮ ቢሮ እና ሽንት ቤት ሲመላለስ ነው ያረፈደው የሚል ምርመራ ጉንጭ አልፋ ወሬ ነው።
– በመጨረሻም የሶስት ልጆች አባት የሆነው ኢ/ር ስመኘው በስንብት መልዕክቱ ላይ የአንዱን ልጅ ብቻ አደራ ለፀሀፊው እና ለራሱ እንዳስቀመጠ ሲናገሩ ለውሸት ውጤት እንኳን እንዳልተዘጋጁበት እና አሁንም የተደበቀ ሴራ በዙርያችን እንዳለ ውልል ብሎ ይታያል።

https://www.facebook.com/fanabroadcasting/videos/1826857917400000/

Filed in: Amharic