>
5:13 pm - Saturday April 19, 8251

በአየር መንገዱ ያላቸውን የበላይነት የማስቀጠሉን ሴራ ስራዬ ብለው ተያይዘውታል!! (ሚኪ አምሀራ)

በአየር መንገዱ ያላቸውን የበላይነት የማስቀጠሉን ሴራ ስራዬ ብለው ተያይዘውታል!!
ሚኪ አምሀራ
* አየር መንገዱ ብዛት ያላቸው የትግራይ ተወላጆች መታወቂያቸውን “አማራ” እና “ኦሮሞ” በሚል እየቀየሩ ከፋይላቸው ጋር በማያያዝ በጭምብል ማንነት ያላቸውን የበላይነት የማስቀጠሉን ሴራ ስራዬ ብለው ተያይዘውታል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሃላፊ አቶ ተወልደ ጫናዉ ሲበዛበት በክልል ከፋፍሎ የአማራ ክልል ሰራተኛ ይበዛል ለማለት በሚመስል ሁኔታ መረጃ አዉጥቷል፡፡ ሲጀምር አዲስ አበባ፤ ድሬዳዋና፤ ሀራሪን አብሮ አማራ ክልል ብሏቸዋል፡፡ በክልል ሳይሆን በዘር ከእነ ስማቸዉ ሊስቱን እንዲያወጣ እንጠይቀዋለን፡፡ አማራ ክልል እነማን ናቸዉ የተቀጠሩት፡፡ አዲስ አበባ ዉስጥ እነማን ናቸዉ የተቀጠሩት፡፡ ባለፈዉ የስልጣን ቦታ የያዙትን እስከ ዘረቻዉ ትክክለኛ መረጃ አዉጥተናል፡፡ ጫና ሲበዛብህ በክልል ሰራተኛ ቁጥር ታወጣለህ፡፡ በዘር አዉጡት እስከስማቸዉ እስከ ትዉልድ ቦታቸዉ፡፡ አዲስ አበባስ የአማራ ክልል ሆነ እንዴ፡፡ አይር መንገዱ በቅርብ ምንድን ነዉ ያደረገዉ፡፡ የትግሬ ካቢን ክሩዎች እኮ የሰራተኛ መቀነስ ሊኖር ይችላል ተብሎ የቀበሌ መታወቂያ አማራ እና ኦሮሞ የሚል እንዲያመጡ ነዉ የተደረገዉ፡፡
ማህደራቸዉ ላይ አዳዲስ መታወቂያ ነዉ እኮ እያስገቡት ያለዉ፡፡ ይህ ሰራተኛ መቀነስ ሲባል በትክክልም አማራና ኦሮሞ የሆኑት ተለይተው ስለሚታወቁ እነሱኑ እየለቀሙ ለማባረር እንዲያመቻቸው ታስቦበት የተሰራ እኩይ ተግባር ነው፡፡ አየር መንገድ የምትሰሩ ዜጎች ይሄን ጠብቁ፡፡ የአየር መንገዱ ቋንቋ እንኳን ባልታወጀ አዋጅ ትግሬኛ ከሆነ ሁለት አስርታት ተቆጠሩ፡፡
ይሄዉ የኢትዮጵያ  አየር መንገድ 18 ኤግዘጊዉቲቭ አሉኝ ከዚህ ዉስጥ ትግሬን 5 ብቻ አድርጎ አዉጥቷል፡፡ እዉነታዉ ይሄዉ ነዉ፡፡ አቶ ተወልዶ መረጃ ኩክ በማድረግ ልታጭበረብር አትችልም፡፡ በክልል አጭበርብረህ ልታልፍ፡፡
1. ተወልደ ገብረማሪያም ( ትግሬ)—-CEO
2. ተክሌ ገብረዮሃንስ (ትግሬ)–MD Ethiopian Ground Services
3. ሚካኤል ያሬድ (ትግሬ)…..VP Customer Service
4. ዮሃንስ ሃይለማሪያም (ትግሬ)–VP Flight Operations
5. ራሄል አሰፋ (ትግሬ)–VP Marketing
6. ዘላለም ተስፋይ (ትግሬ)–MD Ethiopian MRO Services
7. ኢሳያስ ወልደማሪያም (ትግሬ)–MD Ethiopian International Services
8. ፍጹም አባዲ (ትግሬ)-MD Ethiopian Cargo Services
9. ሶሎሞን ደበበ (ትግሬ-ደቡብ) MD Ethiopian Aviation Academy
11. ገናነዉ አሰፋ (አማራ)—VP Legal Counsel & Corporate Secretariat
12. መሰረት ቢተዉ (አማራ)-Chief Financial Officer
13. መስፍን ጣሰዉ (አማራ)Chief Operating Officer
14. ቡስራ አወል (ስልጤ/ደቡብ)Chief Commercial Officer
15. ለኣከ ታደሰ (ኦሮሞ እና አማራ) Chief Information Officer
15. መሳይ ሽፈራዉ (ደቡብ)
16. ሄኖክ ተፈራ (ኦሮሞ እና ደቡብ)
17. ቃሲም ገረሱ (ኦሮሞ)
Filed in: Amharic, Current Affairs / News