>
5:13 pm - Sunday April 19, 3750

ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ዶክትሬት ዲግሪውን እንዳልተማረ አስተማማኝ ማስረጃ አለን! (NEAEA)

ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ዶክትሬት ዲግሪውን እንዳልተማረ አስተማማኝ ማስረጃ አለን!
National Educational Assessment and Examinations Agency-NEAEA
ስለ “ዶ/ር ” ደብረፅዮን  የትምህርት ማስረጃውም መረጃ ስጠን ባላችሁን መሰረት ከመረጃ ቋታችን ትክክለኛውን ማስረጃ ልናቀርብላቸሁ ወደድን፡፡
እኔ ትኩረት ስለግለሰቦቸ ሳይህን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ሲበላና ሲታለል እንደኖረ ማሳየት ብቻ ነው፡፡ መንግስት ደግሞ ከዚህ ማስረጃ ተነስቶ ትክክለኛ የማጣራት ስራ መስራት ይችላል፡፡በእርግጥ በአሁኑ ጊዜ መንግስትን እያስቸገረ ያለው ኃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በመሆኑ ሁኔታዎችንም ለማጣራት እንደሚቸገር መገመትም ይቻላል፡፡ነገር ግን የደብረፅዮንን እንደ መነሻ በመውሰድ ሌሎቸንም ማጣራት ይቻል ይሆናል፡፡
የዶ/ር ደብረፅዮን የዶክትሬት ጉዳይ እንዲህ ነው፤ ደብረፅዮን ኢትዮ ቴሌኮም በሚመራበት ወቅት በፕሮጀክት ስም ከፍተኛ ገንዘብ የሚመራ በመሆኑ ሁሉም የውጪ ሀገር ካምፓኒዎች ዓይናቸውን በሱ ላይ አሳሪፈው ነበር፡፡የፌዴራል መንግስት ከቻይና መንግስት ኢትዮ ቴሌኮምን እንደ ማስያዣነት በመጠቀም አንድ ቢልዮን ስድስት መቶ ምልዮን ዶላር ወይም በአሁኑ የኢትዮጵያ ብር ሃምሳ ቢልዮን ብር ገደማ (50 ቢልዮን ብር ገደማ) ተበድሮ የዘመነ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት አስቦ ነበር፡፡ በዚህም ከፍተኛ ገንዘብ ዜድትኢ (ZTE) እና ህዋዌ (Huawei) የሚባሉ ሁለት ዓለም አቀፍ የቻይና ካምፓኒዎቸ ስራውን እንዲሰሩ ለምርጫ ይቀርባሉ፡፡ዶ/ር ደብረፅዮን ደግሞ አጠቃላይ ፕሮጀክቱን ዜድቲኢ (ZTE) የሚባል ካምፓኒ ብቻ መስራት አለበት ብሎ ከፍተኛ የመሞዳሞድ ስራ ሰራ፡፡ባቃደውም መሰረት ከዚደቲኢ (ZTE) ጋር ጥብቅ ቁርኝት በመፍጠር ህዋዌን (Huawei) ከጨወታ ውጨ አደረገና አጠቃላይ ፕሮጀክቱን ዜደትኢ (ZTE)ብቻ እንዲሰራ ወሰነ፡፡
ህዋዌዎቸም የዋዛ አልነበሩምና በግል ጋዜጦቸ ላይ ደ/ር ደብረፅዮን ከዜደቲኢ ሰዎቸ ጋር በመተባበር አሻጥር በመስራት ሀገር ልበላ እያኮበኮበ ነው የሚል ስሜት ያለው መረጃ በፎርቹን እንግልዘኛ ጋዜጣ እትም አማካይነት መጠዝጠዝ ጀመሩ፡፡በዚህን ጊዜ የደ/ር ደብረፅዮን የቅርብ ሰዎቸ ይህ መረጃ ከወጣ ጥሩ አይሆንምና ፕሮጀክቱን ለሁለቱም የቸይና ካምፓኒ እኩል አከፋፍልና ነገሩን አዳፍነው ብለው መከሩትና ደፂም ምክራቸውን ሰምቶ ለሁለቱም እኩል አከፋፈለ፡፡ ለእያንዳንደቸውም 800,000,000 ዶላር ወይም ወደ ሃያ አምስት ቢልዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብአከፋፈላቸው፡፡
ህዋዌም ፎርቹን ጋዜጣ ላይ የፕሮጀክቱን ሁኔታ በመጠዝጠዝ የ800 ምልዮን ዶላር ስራ አገኘቸ ማለት ነው፡፡ትልቁ መነሻዬ የሰውዬውን የትምህርት ሁኔታ ለመግለፅ ነውና ወደዛው ልመለስ፡፡ዶ/ር ደብረፅዮን ለምን ከዜድትኢ (ZTE) ጋር ጥብቅ ቁርኝት ፈጠሩ የሚለው እጅግ አወዛጋቢ የሚመስል ቢሆንም በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች ግን ጉዳዩን አብጠርጥረው ያውቁታለ፡፡
ዶ/ሩ ከ(ZTE) ጋር ጥብቅ ቁርኝት የፈጠሩት (ZTE)የሚባለው ካምፓኒ ለዶ/ር ደብረፅዮን የገባው ቃል ስላለ ነው፡፡ይህውም ደብረዮን ፕሮጀክቱን ሙሉ በሙሉ ከሰጣቸው ሙሉ የዶክትሬት የትምህርት ወጪውን እንደሚሸፍኑና የቻይና እንጂነሮች ትምህርቱን እንደሚማሩለት እንዲሁም ዶ/ር ደብረፅዮን ደግሞ ለይስሙላ ብቻ በ(ZTE) ወጪ ለትምህርት በሚል ሰበብ እንግልዝ ሀገር ለንደን ከተማ መመላለስ እንደሚችል ቃል ስለተገባለት ነው፡፡በተገባለት ቃል መሰረትም በዶ/ር ደብረፅዮን ስም ዶክትሬቱን የተማሩለት የቻይና እንጂነሮች ናቸው፡፡
Filed in: Amharic