ሌሊሳ ወደ ሀገሩ እንዲገባ ጥሪ ቀረበለት!!!
ከድር እንድሪስ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን እና ኦሎምፒክ ኮሚቴ በጋራ በመሆን ለአትሌቱ ባቀረቡትለት ጥሪ ወደ ሀገሩ ተመልሶ ውጤታማ ስራ እንዲሰራ አጥብቀው ጠይቀዋል።
በሪዮ ኦሎምፒክ እና በተለያዩ ስፖርታዊ መድረኮች ኢትዮጵያን በመወከል ውጤት ያስመዘገበውና በሀገሪቱ የነበረውን ስርአት በመቃወም ጥገኝነት መጠየቁ የሚታወሰው ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ሀገሩ በመመለስ የተለመደ ፍሬያማ ውጤቱን ለሀገሩ አንዲያበረክት ተጠይቋል።