ቻላቸው በቀለ
የዙምባብዌን የምርጫ ሂደት ለመታዘብ ወደ ዛው ያመሩት የቀድሞው ጠ/ምኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት መንግስቱ ሀይለ ማርያምን በሀራሬ ጋንሂል አግኝተው ደምረዋቸዋል።
ግንቦት 13 ቀን 1983 ከኢትዮጵያ የወጡት መንግስቱ በዝንባብዌ ለ 27 ዓመታት ሲኖሩ በወታደር አማካሪነት ለሙጋቤ አገልግለዋል፡፡
መንግስቱ አሁን ምርጫውን ላሸነፉት የዝንባብዌው ፕሬዜዳንት ኢመርሰን ማናጋግዋ ጋርም ወዳጅ እንደሆኑ ይነገራል፡፡
መንግስቱ ሰፊ የእርሻ ማሳ ያላቸው ሲሆን፣የዝንባብዌ ዜግነት አግኝተው በቅንጦት ይኖራሉ፡፡
…
መንግስቱ ሶስት ልጆችን ያፈሩ ሲሆን ፣ሶስቱም የህክምና ዶክተሮች ናቸው፡፡