>

የማለዳ ወግ ... የኢትዮጵያ ትንሳኤ በመንታ መንገድ  !!!  (ነቢዩ ሲራክ)

የማለዳ ወግ … የኢትዮጵያ ትንሳኤ በመንታ መንገድ  !!!
 ነቢዩ ሲራክ.
የትንሳኤው ጅምር ማሳያው ስኬት 
* የትንሳኤው አደናቃፊዎች አጓጉል ህልም
* ዶር አብይ በሀገረ አሜሪካ በፍቅር መንገድ 
* ሳውዲ ላይ እኔ ፣ አሜሪካ እነ ታማኝ ስንከለከል
*  እንዳንጋጭ እንዳንለያይ የእኔ ምክር
  
 
 የትንሳኤው ጅምር ማሳያው ስኬት …
    የኢትዮጵያ ትንሳኤ በመንታ መንገድ ቆማለች !  በሶስት ወራት እድሜ ኢትዮጵያውያን ያላየነው ይሆናል ተብሎ የተገመተ አይደለም ። ሁሉንም እንደ መልኩ በፍቅር የሚመከከቱ መሪ ዶር አብይን በአጭር ጊዜ አስደናቂ እርምጃ የፖለቲካ እስረኞችን በመፍታት ፣ ከተቃዋሚዎች ጋር እርቅ በመፍጠር ፣  ኢኮኖሚው እንዲያንሰራራ በማድረግ ፣ ትውልድ የጨረሰው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት በሰላምና በፍቅር እንዲዘጋ ፣ በሙስሊማንና በክርስትያን የሐይማኖት መሪዎች መካከል የነበረው ጣልቃ ገብነት አቁሞ እርቅ እንዲዎርድ ማድረጋቸው የኢትዮጵያ ትንሳኤ ጅማሮ ምልክቶች ናቸው ባይ ነኝ !
የትንሳኤው አደናቃፊዎች አጓጉል ህልም …
   ከዚህ የአጭር ወራት አስገራሚ ስኬት ኢትዮጵያ ነጋላት ፣ ኢትዮጵያውያን መሪ አገኘን ስንል የስውር ሴራ ቀጠሮ በየአቅጣጫው እየገመደ ይገኛል። በቀናው የሰላም ፣ የፍቅርና የይቅርታ መርህ በእንደመር የተገኘው ህብረትና  ለውጥ እንዳይሳካ ብዙ ፈታኝ ስራ እየተሰራ መመልከት ይዘናል ። ከብዙው በጥቂቱ ልጠቀስ ።  በሰኔ 16 ቀን 2010 ዓም የድጋፍ ሰልፍ መሪያችን ለመግደልና ህዝብን ለማጫረስ  ቦንብ መጣል ፣ በየክልሎች በሚሰራ ርኩስ ሴራ ሰውን በዘር ፣ በሐይማኖትና በጎሳው ማናቆር ፣ ማጋጨት ፣ ከአረብ ሀገራትና ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተደረገውን መልካም ለሀገር የሚበጅ የሁለትዮሽ ግንኙበት ማንቋሸሽ ፣ ትናንት ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓም የህዳሴውን ግድብ ጀግና ኢንጂነር ስመኘው በቀለን መግደል ከሚጠቀሱት ኢትዮጵያን የማጥፋትና የማጨራረስ ተንኮል ሴራ ሆኖ እያየን ነው  🙁
 ይህ ደስታችን ሳናጣጥም የሚከወን ስውር ሴራ የሀገራችን የኢትዮጵያ ትንሳኤ በመንታ መንገድ ቆማ እንድናያት አድርጎናል!  ጥፋት የሚያሴሩልን ወደ መልካም የምንጓዝበተረን መንገድ ለማደናቀፍ  ክፉዎች ያደረጉት ሴራ ከሐጢያቱ ሁሉ የከፋ ሐጢያት ነው ባይ ነኝ  ! ህብረታችንና ለውጣችን ማየት የማይፈልጉት ወገኖች ሴራ ሀገር የማወክ የማፈራረስ ህልም ዋጋው ከባድ ቢሆንም ኢትዮጵያውያ አትጠፋም !
በአሜሪካ ኢንባሲው የዶር አብይ ክስተት ያስደመመኝ !
  በመሪሩ ሀዘን መካከል የፍቅር ሰላምና ይቅርታ መንገድ ተከታዩ ዶር አብይ በአሜሪካ ኢንባሲ ንግግራቸው ” አፍሪካ መሪ አጥታ ለማኝ ሆናለች  …” ብለዋል ። ንጉሱ ዶር አብይ ” ፍቅር ያሽንፋል ፣ ፍቅር ያሸንፋል! ” ያሉት  ዶር አብይ አህመድ ” የፈረሰ ቤታችን እንስራው! ” በሚል መሳጭ ንግግር አድርገዋል ።
    ድንቁ የፍቅር መሪ ንግግራቸውን እንደጨረሱ እንግዶችን በመቀመጫቸው እንዳነሱ በመጠየቅ ” እየዞርኩ ሰላም እላለሁ ” አሉና አስደመሙን ። ቃል አክባሪው ዶር አብይ በቃላቸው መሰረት በየጠረጴዛው እየዞሩ ለተጋባዦች ያላቸውን ክብር አሳይተዋል።
 ሳውዲ ላይ እኔ ፣ አሜሪካ እነ ታማኝ ስንከለከል …
   ዶር አብይ ንግግራቸውን  እንደጨረሱ ይህኔ ትዝ ያለኝን አንድ የቅርብ ወራት ትዘታ ልግለጠው ። ዶር አብይ ሳውዲ መጥተው በነበረ ወቅት እኔ እንዳላገኛቸው ተደርጎ ነበር። ዳሩ ግን ስለሚሆነው ሁሉ መረጃ ያላቸው ብልሁ ዶር አብይ   አምባሳደር ውብሸት ደምሴን ጠርተው ነቢዩ ሲራክን አገናኝ በማለት በአንባሳደሩ ስልክ አስደውለው አገኝተውኛል ። በስልክ በነበረን ቆይታ  ፍጹም ትህትና በተሞላበት መንገድ ስለብላቴናው መሐመድ መረጃ እንዳላቸው በመግለጽ እኔም ሆንኩ የብላቴናው አጋሮች ስላደረግነው የፍትህ ጥያቄ ማሰማት ድጋፍ ምስጋና አቅርበውልን ነበር  !
    በምድረ አሜሪካም ኢንባሲው እነ ታማኝ ታግደው ነበር ። የዲሞክራሲ ታጋዮች መገለል ያንገበገባቸው አንድ ወንድም ከተጋባዥ ታዳሚዎች መካከል ዶር አብይ ንግግራቸውን እንደጨረሱ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው  “ታማኝ ለምን አይገኝም?” በሚል የታማኝን ክልከላ በመቃዎም የዜጋ ጥያቄያቸውን አሰምተዋል  ። ዶር አብይ አህመድ መለሱ  “ታማኝ፣ ሲሳይ አጌና፣ አበበ  በለው ፣ አንዳርጋቸው ጽጌ … ሁሉም ይኖራሉ” ሲሉ መለሱ  ! ለመረጃ ሰው ለዶር አብይ አህመድ እውነት አትጠፋበትም ፣ ፈልጎ አግኝቷታል ! በነገራችን ላይ ሳውደ ጅዳም በተደረገው ድጋፍ  የሆነው ይህው ነው …
 ኢትዮጵያና ህዝቧም በእኩዮች ሴራ እንዳንጋጭ ! 
    በመጨረሻም የኢትዮጵያ ትንሳኤ በመንታ መንገድ ላይ ናቸውና ለኢትዮጵያና ህዝቧ የተሻለውን የለውጥ ጅማሮ ለማስቀጠልና በእኩዮች ሴራ እንዳንጋጭና እንዳንለያይ የበኩሌን ልበል ።  ከምንም በላይ የክፉዎችን ሴራ ለማክሸፍ ተረጋግቶ የሂደቱን አደናቃፊዎች የመከላከል ፣ ሀገር ህዝብ የመከላከል ኃላፊነት አለብንና  የተጀመረው የለውጥ ጅምር በሴረኞች እንዳይደናቀፍ አላስፈላጊ ሰላማዊ ሰልፍን እናስወግድ ። ዘርን ተኮር ጸብ አጫሪ መረጃ አናሰራጭ ። የመንግስትም ሆነ የግለሰብን ንብረት አናውድም ፣ አናቃጥል ። ከመቸውም በላይ ዛሬ ክፉ ቀንን ከሚመኙልን መረብ ላለመውደቅ በጉዳት ስሜት የተቆጣውን ወገናችን  ተረጋግረን ህዝባችን እናረጋጋ ! በቃ አማራጩ መንገድ ይህ ነው !
     ኢትዮጵያ ወደ ትንሳኤው በምታደርገው ግስጋሴ ላይ በክፉዎች ተጠልፈው ህይዎታቸውን ላጡት ለኢንጂነር ስመኘው በቀለና እና የቀሩት ወገኖችን ነፍስ ይማር 🙁 ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ: ( አሁንም በሴራው የተፈናቀሉ ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸውና የተለያየ መስዋዕትነትን ለከፈሉ ወገኖች ክብር እሰጣለሁ  !   
ፈጣሪ ሀገራችንና ህዝቧን ይጠብቅ  !
ሐምሌ 20 ቀን 2010 ዓም
Filed in: Amharic