>

ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጅቱን የጠናቀቀው የሽብር ቡድን!!! (ከድር እንድሪስ) 

ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጅቱን የጠናቀቀው የሽብር ቡድን!!!
ከድር እንድሪስ 
* በስዩምመስፍን የሚመራ ከ3ሺህ በላይ የሽብር ሰራዊት ስልጠና እየወሰዱ ይገኛል
 
 ሰራዊቱ “ደርግ/አማራ መጥቶብናል ሊያጠፋን ስለሆነ ተዘጋጅ”  ተብሎ የተሰበሰበ ነው
ለጥንቃቄ የወጣ ሚስጢራዊ መረጃ
 
ለውጡን ለመቀልበስ ሌት ተቀን  የሚባዝነው ሀይል አሁንም የሽብር ጥላውን በኢትዮጵያ ላይ አጥልቷል።
አዲሱን አገራዊ ለውጥ ለመቀልበስ ጌታቸውአሰፋንና ከመከላከያ የተሰናበቱ  የህወሃት ጀነራሎችን ማዕከል አድርጎ የሚቀሳቀሰው የፀረ-ለውጥ ቀልባሽ ሀይል የሽብር ጥቃቶችን፣ ከትግራይ ክልል ውጭ መላ አገራችን አስፋፍቶ ለመቀጠል ወስኗል ።
የፀረ-ለውጥ ሽብር ቡድኑ በግላጭ በአደባባይ ከተፈፀመው የሰኔ 16ቱ ሽብር ጥቃት በተጨማሪ በተለያዩ የአገራችን ልዩ ልዩ አካባቢዎች እያስፈፀመው ያለው ፍጅት ስንታዘብ ቆይተናል፡፡
 አሁን ደግሞ ማዕከሉን መቀሌ ያደረገው ይህ የሽብር ቡድን ሌላ ዙር ሽብርና ብጥብጥ ዘመቻዎችን ለማከናወን በከፍተኛ ሚስትር ዝግጅት ላይ እንዳለ የተገኙ መረጃዎች በመጠቆም ላይ ናቸው፡፡
የመረጃ ምንጮች እንደሚጠቁሙት ከሆነ 
“ትግራይ ክልል ማይፀብሪ በሚባል ቦታ፣ ከአማራ ክልል ጋር በሚያዋስኑ አካባቢዎች የሚገኙ ሥራ አጥ የሆኑ ከሶስትሺህ የሚያልፉ ወጣቶችን በመመልመል፣ የሰርጎ ገብ ውጊያ፣ የከተማ ውጊያና እና የተቀጣጣይ ፈንጅ አጠቃቀም ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡”
“በ29/10/10 ዓ.ም ለዚህ ስልጠና የሚውል የጦር መሳሪያና ፈንጅ በሁለት ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ታጭቆ ወደ ማሰልጠኛ ገብቷል፡፡”
”ይህንን በከፍተኛ ሚስጥር የተያዘ ኦፕሬሽን የሚፈያስፈፅሙ አካላት “ደርግ/አማራ መጥቶብናል ሊያጠፋን ስለሆነ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ ይኖርብናል” የሚል የሀሰት ፕሮፖጋንዳ በማሰራጨት፣ ከአማራ ክልል ጋር በሚዋሰኑ አጎራባች የትግራይ አካባቢዎች ህዝብ ለጦርነት እንዲነሳ ቅስቀሳ በማድረግ፣ መጠነ ሰፊ የሆነ እስካሁን ምንጩ ያልታወቀ የጦር መሳሪያ ትጥቅ፣  የማስታጠቅና የማሰልጠን ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡“
ለዚህ የሽብር ተግባር ተብሎ በአጭር ግዜ በተደራጀው “ #አግበ” በሚሰኝ ጊዜያዊ የወታደራዊና የሽብር ጦርነት ማሰልጠኛ፣ በ30/10/10 ዓ.ም የሽብር ዘመቻው ዋና አደራጅ ፣ የህወሃቱ አቶ #ስዩምመስፍን ሰብሳቢነት በአንድ ዙር 618 ሰዎች በአጠቃላይ ለ4 ዙር በድምሩ ከ3ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች የሽብር ስልጠና እየወሰዱ ይገኛል፡፡
 ስልጠናው፣ ከኢህአዴግ የአመራር ምርጫ (ከመጋቢት 20) በፊት ለጦርነት ዝግጁ እንዲሆኑ በሚል እየተሰራበት የሚገን ሲሆን ዝግጀቱ ”ለአነስተኛና ጥቃቅን ስልጠና“ የገቡ በሚል ሽፋን የሚሰጥ ነው፡፡
 በስልጠናው ዋና ዋና የህወሃት ወታደራዊ፣ የደህንነትና ሲቪል የቀድሞ ባለስልጣናት የሚሳተፉበት ሲሆን፣ በተጨማሪ ስልጠናውን የሚያከናውኑት ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ከሰራዊቱ የተቀነሱ፣ ያኮረፉና በተለያየ ስፍራ በግዳጅ ላይ ያሉ በፍቃድ ምክንያት ከክፍላቸው ወጥተው በዚህ ስፍራ እየተገኙ በአንድ ዙር ለ18 ቀን የተለያዩ ስልጠናዎችን እንደሚሰጡ የመረጃ ምንጮች ይገልፃሉ፡፡
የዚህ ሁሉን አቀፍ የሽብር ሴራ እቅድ እጅግ አደገኛና፣ አስደንጋጭነት የሚጎላው፣ ሴራው #በሰራዊቱ ውስጥ ያደራጀው #የሰርጎ #ገብ #ህዋስ ነው፡፡ የተገኙ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የፀረ-ለውጥ ሀይሉ ወኪሎች “በሰራዊቱ ውስጥ መጠነ ሰፊ የሰርጎ ገብ ህቡዕ መረብ በመዘርጋት፣ የሰራዊቱን ቁልፍ የዘመቻና የሎጀስቲክ መዋቅር ይዘዋል፡፡ በሰራዊቱ ውስጥ የሰረገው ቡድን አገናኝ በመሆን እንደሚሰሩ ይጠረጠሩ የነበሩትና በተጨባጭ ግንኙነት በማድረግ እና የተለያዩ የህቡዕ ስራዎችን በማከናወን ላይ ከሚገኙት መካከል ኮ/ል #ሀጎስ እና ኮ/ል #ዮሀንስ ይጠቀሳሉ፡፡
በፀረ-ለውጥ ሀይሉ በኢትዮጵያ ላይ ባወጀውን ሽብር ጦርነት በመምራትና በማደራጀት፣ በግንባር ከደምትነት እየሰሩ የሚገኙት፣ የቀድሞው የሜቴክና የኢንሳ ሀላፊ የነበሩት ጀነራል መኮንኖች ማለትም ሜ/ጀ #ክንፈ እና ብ/ጀ #ተክለብርሃን/ሳንቲም/ በየሳምንቱ በመከላከያ ታርጋ በምትንቀሳቀስ፣ #ጥቁር #ኮብራ ተሸከርካሪ በጅቡቲ መቀሌ መስመር ሰርዶ በሚባል ስፍራ በመመላለስ ላይ ሲሆኑ በተደጋጋሚ እነሱ ከተመለሱ በኋላ በርካታ ተሸከርካሪዎች ሳይፈተሹ በቀጥታ ወደ ትግራይ በመግባት ላይ መሆናቸው በመረጃ ተጠቁሟል፡፡
ለምሳሌ፡ በሁለት ዙር  የመጡ፣ የመከላከያ ሰሌዳ ያላቸው 28 ቮልቮዎች በተደጋጋሚ ጋላፊ ባለው ጉሙሩክ ሳይፈተሹ እንዲያልፉ ተደርጓል፣ ምን እንደጫኑ የማይታወቁ፣ በርካታ የግል ተሸከርካሪዎችም፣ በገፍ በመግባት ላይ መሆናቸውን መረጃዎች በማመልከት ላይ ናቸው፡፡
በዚህ ወቅት መቀሌን የእዝ ማእከሉ አድርጎ በመላው አገራችን የጥፋት ሰንሰለቱን የዘረጋው ፀረ-ህዝብ ፀረ-ለውጥ ሀይል፣ ከዚህ ቀደም ያልታየ ሚልኖችን ለፍጅትና ስደት የሚዳርግ እልቂት እየደገሰ መሆኑን ህዝብ አውቆ አካባቢውን በንቃት እንዲጠባበቅ ማሳሰብ ያስፍጋል፡፡
 መንግስት ከምንም ነገር በላይ የህዝብን ደህንነት የማስጠበቅ ሀላፊነት ያለበት በመሆኑ ከህዝቡ ጋር ተቀናጅቶ በመስራት፣ አገር በማራቆት ባከማቹት ምቾት ታውረው አገር ለማጥፋት የተነሱ የቀን ጅቦች እኩይ ፍላጎት እንዳይሳካ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡  “
 Very much credible source
Filed in: Amharic