>

"እኛም ሰው ነን አላስፈላጊ እርምጃ እንድንወስድ አታስገድዱን" (ዶ/ር ዓቢይ አህመድ የመጨረሻ የሰላም ጥሪ) 

“እኛም ሰው ነን አላስፈላጊ እርምጃ እንድንወስድ አታስገድዱን”
ዶ/ር ዓቢይ አህመድ የመጨረሻ የሰላም ጥሪ 
ጆሮ ያለው ይስማ ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ በአንዳንድ አካባቢዎች ግጭቶችን ለሚፈጥሩ የቀን ጅቦች ወደ ሰላም እንዲገቡ የመጨረሻ የሰላም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ኢትዮጵያ ውስጥ ዛሬም በሚያሳፍር ሁኔታ ሰዎች ይሞታሉ” በማለት ንግግር ያሰሙ ሲሆን ይህ እንዲያበቃም “እባካችሁ ወደ ሰላም ግቡ፤ ይህ የመጨረሻ የሰላም ጥሪዬ ነው” ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ እና በአስመራ መካከል ያለው የጥላቻ ግንብ መናዳን አንስተው በአንዳንድ ክልል ያለው “የሳር ቀጤማ ግንቦች ይፍረሱ” በማለት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የዛሬው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ይዘው የመጡት ፍቅር በ50 ቢሊየን ብር የማይገዛ ውድ ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም ዛሬ የተቀደደው ጥቁር መጋረጃ ነው የሚበጀን ፍቅርና ሰላም ብቻ ነው….፡፡
በተጨማሪም የሰላም ዋጋው ያልገባቸው አካላት በአንዳንድ አካባቢዎች ግጭቶች እንደሚያስነሱ ጠቅሰው ዛሬ እንኳ ስለ ሰላም ተማሩ በማለት ጥሪ አቅርበውላቸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰዎች ሞት ማብቃት አለበት ያሉ ሲሆን የሰላም ጥሪያቸውን አጽንዖት በመስጠት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመጨረሻም አልፎ አልፎ የምታውኩን ሰዎች ፍቅራችንን ባታበላሹት መልካም ነው ነገርግን ግጭቶች በዚህ የሚቀጥሉ ከሆነ ሰውነንና ወዳልተፈለገ ነገር እንዳታስገቡን አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
Filed in: Amharic