>

የባህርዳር ሰልፍ በኔ በአንድ ትግራዋይ እይታ! (ናትናኤል አስመላሽ)

የባህርዳር ሰልፍ በኔ በአንድ ትግራዋይ እይታ!

(ናትናኤል አስመላሽ)

የባህርዳሩን ሰልፍ አየሁት፣ በጣምም ተገረመኹኝ፣ ብአዴን ሙሉ በሙሉ ከድሮ የህውሓት ተላላኪዎቹ ባይጸዳም፣ በሰልፉ ተገኝቶ ለለውጡ አጋር መሆኑን እና ዋና ተዋናይ መሆኑን በም/ል ጠ/ሚ እና በክልሉ ፕሬዝዳንት ደጋግሞ ጠቅሰዋል። ብአዴን አመራር በተለይ ገዱ አንዳርጋቸው ህውሓቶችን እንዲህ ሲል ይገልጻቸዋል “ሽንፈታቸው መቀበል ያቃታቸው የኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች” ገዱ ከልቡ ከሆነ ጨዋታው ገብቶታል ማለት ነው! የትግራይን ህዝብ እና ህውሓትን ለይተዋል፣ በጣምም እናመሰግናለን።

እኔ እንደ ትግራዋይ ግን፣ ሰልፉ ባየሁ ቁጥር የትግራይ ህዝብ ለዚህ አለመታደሉ ውስጤ ያለቅሳል”የኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች”(ህውሓቶች) የትግራይ ህዝብ ከሌላው ህዝብ ነጥለው፣ ለማጣላት፣ ለማዋጋት የሚያደርጉትን ጉዞ ሳይ ከዚህ ቦሃላም የትግራይ ህዝብ ለኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች ብሎ ገና ብዙ ዕዳ እንደሚከፍል ይታየኛል። ለኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች ስልጣን ላይ ለመቆየት ተብሎ የትግራይ ተወላጆች በወሎ በባቲ የማይገባ መስዋእትነት እየከፈሉ ይገኛሉ። የኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች የትግራይ ህዝብ ጸረ ኢትዮጲያ ህዝብ ለማሰለፍ በአማራ ክልል፣ በደቡብ ክልል ገንዘባቸውን አፍስሰው ትናንት ደደቢት በነበሩበት ጊዜ የቀለባቸውን ህዝብ እንዲገደል፣ ንብረቱ እንዲወድም እና ሌላውን ቢሄር እንዲጠላ እያደረጉ ነው!

ህውሓቶች ቂመኞች! እባቦች! ከመሆናቸውም ጭምር፣ልባቸው ለፍቅር ሳይሆን ለቂም ብቻ የተፈጠረ ስለሆነ፣ ገዱ ለወ/ሮ እማዋይሽ፣ ጀነራል አሳምነው ሲያቅፍ፣የኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች ለአቶ ገብሩ አስራት፣ ለወ/ሮ አረጋሽ አዳነ፣ ለዶ/ር አረጋዊ በርሀ የፍቅር፣ የይቅርታ ልባቸውን እስካሁንዋ ሳአት ድረስ ክፍት አይደለም። ወ/ሮ እማዋይሽ ከገዱ አንዳርጋቸው ጎን ተቀምጠው ሳይ፣ የዓረናዋ የሽብርተኛ እስረኛ አደይ አልጋነሽ እና የአስራሰባት አመት ፍርደኛ (እስረኛ) ወጣት ፍስሃጽዮን ተኽለሃይማኖት ከደብረጽዮን፣ከስብሓት ጎን አለማየቴ አዝናለሁኝ ውስጤም ያለቅሳል። ጀነራል አሳምነው ከም/ል ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን ጎን ሳይ፣ እድሜ ልክ የተፈረደበትን የዓረና ትግራይ እስረኛ(ፍርደኛ) አቶ ገብረእግዝአብሄር ታደሰ ከስዩም መስፍን ጎን አለማየቴ አዝናለሁኝ አለቅሳለሁኝም።.

. ስለዚህ የትግራይ ወጣት ምርጫው አንድ ነው! የኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች በአመጽ ከስልጣን ገፍትሮ ከቀሪው የኢትዮጲያ ህዝብ ጋር መደመር ወይንም ደግሞ፣ ለኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች ተገዢ ሆኖ ስቃዩን፣ መከራው፣ በህውሓት የሚቀነባበረው የዘር ጥቃቱን አሜን ብሎ መቀበል ነው። የትግራይ ህዝብ ለኣሮጌ ዘመን ቁማርተኞች ብሎ መስዋእትነት መክፈል የለበትም! የትግራይ ወጣት ሆይ ስጋትህ ይገባኛል፣ ለትግራይ ህዝብ ግን ትናንትም፣ዛሬም ነገም ከህውሓት በላይ ሌላ ጠላት የለውም አይኖረውምም!!! .

በፎቶ የምትመለከቷቸውየዓረና ትግራይ አባል በመሆናቸው ብቻ; የእድሜ ልክ ፍርደኛ (እስረኛ) አቶ ገብርእግዝአብሄር ታደሰ እና የአስራሰባት አመት ፍርደኛ (እስረኛ) ወጣት ፍስሃጽዮን ተኽለሃይማኖት።

Filed in: Amharic