>

ለአዲስ አበባ ለሚገኙ ወገኖቼ ስለ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ያለኝ ልዩ መልክት (ፕ/ር አለማየሁ ገብረማሪያም)

 ለአዲስ አበባ አንባቢዎቼ  ለጓደኞቼ ለደጋፊዎቼ ለአዲስ አበባ ወጣቶች እና ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ወንድሞቼ እና እህቶቼ:
ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ለያንዳንዳችሁ በግል  የምፅፍላችሁ ደብዳቤ ነው ብላችሁ ተገንዘቡልኝ።  ይህን መልክት የማስተላልፍላችሁ ምክንያት ትልቅ ዉለታ ለመጠየቅ ነው ።
በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ በሚደረገው ለጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ አህመድ የህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ እኔ መገኘት ስለማልችል በኔ ስም ተገኝታችሁ መልክቴን  ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ አንድታደርሱለኝ ነው።
ከናንተ ወንድሞቸና አህቶቼ ጋር ሆኘ ድጋፌን ለትቅላይ ሚንስትሩ መልካም መሪነት ብገልፅ እንዴት ደስ ባለኝ ነበር። ግን ጊዜው አልፈቀደም ።
እንደምታውቁት ላለፉት አስራ ሶስት አመታት ለናንተ ድምፅ ሆኘ ለዓለም ህዝብ ስለ ስቃያቹና ምሬታችሁ በየሳምንቱ አንድ ሳላዛንፍ ሳስረዳሳተምር  ቆይቻለሁ።
እያንዳንዳችሁ — ፅሁፌን ያነበባችሁ ቃለ መጠይቀን ያደመጣችሁ  በኢትዮጵያ ሰባዊ መብት ጉዳይ የፖልቲካ እስረኞች መፈታት ጉዳይ መልካም አስተዳደር ጉዳይ እንዲሁም ስልጣን አላግባብ ለሀያምስት ዓመት ስያጎድሉ  ለኖሩት እውነቱን በመናገር ለምታቁኝ ሁሉ —  በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ ወጣችሁ እኔን ወክላችሁ የእኔ ድምፅ እንድትሆኑለኝና መልእክቴን ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ እንድትሰጡልኝ በትህትና እጠይቃለሁ ።
መልክተም ይህ ነው ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ  – ላሎት የሰላም የእርቅና የፍቅር  በጠቅላላ አነጋገር ኢትዮጵአዊነት ለሚያደርጉት ጥረትና ልፋት ከጎኖ አጠገቦ እገኛለሁ ሙሉ በሙሉ ድጋፌን እስጦታለሁ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ  ንገሩልኝ – ላንዴም ለዘላለምም በኢትዮጵያ የዘር የጎሳ የመከፋፈያ ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት አብሬዎት እቆማለሁ ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከርሶ ጋር ማንዴላ  መልካምነትና እርቅ የሚባል መንገድ የሰየመልንን ይዤ  አብረዎት እጉአዛለሁ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ  ንገሩልኝ – ሰውነታችንና  አንድነታችን ጥላቻንና ዘርነትን ያሸንፋል የሚለዉን እምነቶን ሙሉ በሙሉ እካፈላለሁ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ  ንገሩልኝ – መልካሙ መፅሐፍ እንደሚለው “ጠላቶቻችን ባንድ መንገድ ይመጡብናል ግን በሰባት መንገድ ከፊታቺን ይበተናሉ።”

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ  ንገሩልኝ  – ከመንደር አንስተን ከትንሽ እስከ ትልቅ ከተማ እስከ ሰፊ አካባቢ የሰላምና የእርቅ ዘመቻ እናካሂዳለን ። በራሳችን ጉልበትና እግዚአብሔር በሚሰጠን ማለቂያ የሌለው ኃይል  የሰላምና የእርቅ ዘመቻ እናካሂዳለን ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ  ንገሩልኝ – ይምጡ ይከተሉን ወፊት  በአንድነት ኃይል  በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጠንካራ መንፈስ ስንራመድ ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ያቺ ኢትዮጵያ መሬት ላይ ወድቃ የተጨፈለቀች  እውነት ለትንሣኤ ደርሳለች ።

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ  ንገሩልኝ  – የጋናው ፕሬዚደንት ቅዋሜ ንክሩማ ላፍሪካ አንድነት ድርጅት ያሉትን እደግምሎታለሁ “የኢትዮጵያ ትንሣኤ እየደረሰ ነው።”

ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከርሶ ጋር ሆነን ያቺ ዉድ ኢትዮጵያ የምትባለዋን አገር በኮረብታው ላይ ለመገንባት ዝገጁ ነን ።  በሷም መንገዶች ላይ ፍትህ እኩልነት ሰባዊ መብት የሕግ በላይነት እንደጎርፍ ዉሃና እንደ ታላቅ ወንዝ ይፈስባታል ።

አስታውሱ እንዳትረሱ ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩለኝ — እንወዶታለን ፍቅር  ሁሉን ያሸነፋል!

እባካችሁ እባካችሁ ወገኖቼ  በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ ወጣችሁ የእኔ ድምፅ ሁኑልኝ።

የናንተው

ዓለማየሁ

ኢትዮጵያዊነት  ዛሬ 

ኢትዮጵያዊነት ነገ   

ኢትዮጵያዊነት ለዘላአም ! 

Filed in: Amharic