ባድመ ለኢትዮጵያውያን ከቁራጭ መሬትነት አልፋለች የወጣቶቻችን ደም የእኩዮቻችን አፅመ ርስት የመስዋዕትነት ሀውልት ናት “ለሰላም ሲባል”ቢሆን እንኳን ልጆቹን ለሀገር ሉአላዊነት የገበረው ህዝብ መወያየት አልነበረበትም?
ለባድመ ሲባል እድሜያቸው ያልደረሰ ህፃናት ሌላ ሰው ኪሎ እየተለካላቸው ወደ ጦርነቱ ገስግሰዋል ተከብረሽ የኖርሽው…… እየተዘመረ ወጣት የጥይት ማብረጃ ሆኗል ጉዳዩ የእነዚህ ልጆች መስዋዕትነት ጉዳይ ነው
ጭብጨባ ለዘላለም ይኑርና የአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አጨብጫቢዎች የተሳሳተው መለስ እንደሆነና አሁን ምንም አማራጭ እንደሌለ ሊነግሩን ይፈልጋሉ መለስማ የስህተት አባት ነበር ብዙ አውቆ የተሳሳታቸውን የስህተት ውሳኔዎች አሸክሞን ሔዷል ታዲያ የለውጥ ሀይል ነው የሚባልለት የአብይ ቲም የክፉው መለስ ስህተቶችን እያፀደቀ ነው ለውጡን የሚያሳልጠው??