ፌዴሬሽኑ ባወጣው መግለጫ ላይ፤ 1ኛ- ጥያቄው የቀረበው ዝግጅቱ ሊጀመር ጥቂት ሳምንታት ሲቀረው በመሆኑ፤
2ኛ- በስቴድየም ውስጥ ሊኖር የሚችለው ጭንቅንቅ ታሳቢ በማድረግ፤
3ኛ- ፌዴሬሽኑ ለህዝቡ ደህንነት የሚገባው የኢንሹራንስ ክፍያ ተፈጽሞ ያለቀ በመሆኑና አሁን እንደአዲስ ሁሉንም ነገር መጀመሩ አስቸጋሪ ሊሆን እንደሚችል በመግለጫው ላይ አሳውቋል። ሆኖም ፌዴሬሽኑ ለመጀመሪያ ግዜ፤ የኢትዮጵያ መሪ በዝግጅቱ ላይ እንዲገኝ መጠየቁ በራሱ መልካም ጅምር መሆኑንና ወደፊት በጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ እና በፌዴሬሽኑ መካከል ያለው ግንኙነት እንደሚቀጥል ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን በመግለጫው ላይ አሳውቋል።
አሁን የጨዋታው ኳስ ወደ ዶ/ር አብይ አህመድ እና ወደ ህዝቡ ተመልሷል። ስለዚህ የስፖርት ፌዴሬሽኑን ውሳኔ ኢምባሲው እና ዶ/ር አብይ አህመድ በማክበር ሊቀበሉት ይገባል። ከምንም በላይ ደግሞ ህዝቡ የ31 ቡድን ተወካዮች ያሉበትንና ሃሳባቸውን በነጻነት አንሸራሽረው ድምጸ ውሳኔ የሰጡትን የአብላጫ ቦርድ አባላት ድምጽ ማክበር ይጠበቅበታል። እኛን ጨምሮ ብዙዎች የዶ/ር አብይ አህመድን በዳላሱ ዝግጅት ላይ መገኘት የምንደግፈው የነበረ ቢሆንም፤ የአብላጫ ድምጽ ውሳኔ መከበር ስላለበት፤ ፍላጎታችንን ለራሳችን ዋጥ አድርገን፤ የፌዴሬሽኑን ውሳኔ ግን ልናከብር ይገባናል – መልእክታችን ነው።
የድምጹ አሰጣ ጡም እንዲህ ነበር። የጋዜጠኛ አርአያ ተስፋማሪያምን ጽሁፍ ያንብቡ