>
5:13 pm - Sunday April 19, 2336

በህወሀት ወታደሮች የተፈጸመ ወሲባዊ ጥቃት እና አሰቃቂ ግድያ!?! (በዳግማዊ ኡመር ፋርዳ)

ግዜው በደርግ መንግሥት ዘመን ነው የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ መንግሥት  ከመቋቋሙ ጥቂት ዓመታት በፊት!የኢትዮጵያ አብዮታዊ ሠራዊት አባል የኾነ አንድ ዋልጌ ወታደር ፣ አንዲት የመቀሌ ከተማ ነዋሪ ላይ ፣ አስገድዶ የወሲብ ጥቃት ይፈፅምባታል ፤ ጉዳዩ በከተማው ውስጥ የነበረው ሠራዊት የበላይ አዛዦች ጋር ይደርሳል፤ አዛዦቹ ጀነራሎች ለውሳኔ አልተቅለሰለሱም! አልተልመጠመጡም! አልወገኑም! ግዜ አልፈጁም! ወዲያውኑ ሕዝብ በአደባባይ እንዲሰበሰብ ጥሪ አስተላለፉ፤ ሕዝቡም ተሰበሰበ፤ ወንጀለኛው ወታደርም በህዝብ ፊት ቀረበ ፤ አዛዥ ጀነራሎች “እከሌን ያየህ ተቀጣ!” ብለው
_
 በጥይት ተቀጥቅጦ እንዲገደል የወሰኑት ውሳኔ ተግባራዊ ተደረገ ፤ ወታደሮች የጠብመንጃቸውን የእሳት መለኮሻ ምላጭ ደግመው ደጋግመው ሳቡ ፤ በወንጀለኛው ወታደር ላይ የጥይት ጎርፍ ለቀቁበት ፤ ጭንቅላቱ ተበርቅሶ ፣ ጀርባው ወንፊት ሆኖ በሕዝብ ፊት ተገቢውን ቅጣት ተቀብሎ ተገደለ! ሕዝቡም የደርግ መንግሥትን አመሰገነ ! እርምጃው አዲስ አበባ ካሉት ሊቀመንበሩ ዘንድ ደረሰ ፤ ” ደግ አደረጋችሁ!!!” አሉ ፤ የደርግ መንግሥት ከትግራይ ክ/አገር ለ 17 ዓመታት ስሙኒ ሳንቲም ግብር አልሰበሰበም!!! 17 ቀኖች ወይም ወሮች አይደሉም ! 17 ድፍን ዓመታት!!! ከዚህ በተጨማሪም አጤ ኃይለሥላሴ የደበቀውን የትግራይ እና የወሎ ህዝብ ረሀብን ለመላው ዓለም ያጋለጠው የደርግ መንግሥት ነው ፤ የወታደራዊው መንግሥት ግብረገብነት ከዚህም ይልቃል! የኢትዮጵያ አብዮታዊ ሠራዊት ፍጹም ጨዋነት ከዚህም ይልቃል ፤ ዛሬ ግን በዘመነ ድንቁርና ህወሓት ፣ ያንን ምስኪን ሠራዊት አለግብሩ ቆሻሻ ስም ተለጥፎበታል ፤ ይህንን አለምክንያት አልጻፍኩም ፤በምክንያት ነው ! ከሥር የምትመለከቷት እህታችን አያንቱ ሙሀመድ ትባላለች ፤ የሀረርጌ ቆቦ ከተማ ነዋሪ ናት ፤ ባለትዳርና የ 7 ወሮች እርጉዝ ነበረች ፤ በትላንትናው ዕለት በአግአዚ ሠራዊት አጠገብ ” አገር አማን ” ብላ ታልፋለች ፤ ወታደሮቹ ለቅኝት የተላኩ እንጂ ፣ በእሷ ላይ የሞት ደብዳቤ ይዘው መምጣታቸውን አላስተዋለችም! ወታደሮቹ በግዳጅ የወሲብ ጥቃት ሊፈፅሙባት ሲሞክሩ ” ኧረ የሰው ያለህ! ኧረ የሕግ ያለህ ድረሱልኝ!” ብላ ጮኸች ፤ በዚህን ወቅት አውሬዎች ባነገቱት ጠብመንጃ እሳት ግንባሯን አነደዱት ፤ እስከወዲያኛው አሸለበች! ሁለት ነፍስ በዘግናኝ ሁኔታ ገደሉ ፤ ወታደሮቹ ይህንን በማድረጋቸው ዛሬ ላይ ምንም የተወሰደባቸው የቅጣት እርምጃ የለም! ቢበዛ ቢበዛ ወደሌላ የግድያ ቀጠና ቢቀየሩ ነው ፤ ነገ ግን የግፉአን አለኝታ የኾነው የጉልበተኞች ሁሉ ጉልበተኛ አላህ ፣ ያልጠበቁትን መዓት እነሱ ላይ እና ፣ ግርድና የቆሙለት አረመኔ መንግሥት ላይ ያወርዳል!!!
 ግን ግዜአችሁ ቀርቧል ፤ ደም እንባ የምታለቅሱበት ግዜ ቀርቧል ፤ አብይ አህመድ ሆይ ብልህ ከሆንክ በግዜ እንደ ኃይሌ መልቀቂያ አስገባ! ከተጠያቂነት አታመልጥም ፤ ጊዜ ለኩሉ ፤  የደርግ እና ህወሓት መንግሥት ልዩነቱ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ፤በተረፈ  እህቴ ሆይ አላህ ጀነቱል ፊርደውሰል አዕላ ማረፊያሽን እንደሚያደርገው ጥርጣሬ የለኝም! ሸሂድ ነሽ ፤ የጀነት ምንጣፍ መላኢካዎች ያንጥፉልሽ! የጀነት መዓዛ እመቃብርሽ ዘንድ አለማቋረጥ ይግባ ፤ ባል ሆይ! ሰብር አድርግ ፤ የትክክለኛ ሷቢር ምንዳ ጀነት ነው! ስብራትህን አላህ ይጠግንልህ!!!
Filed in: Amharic