አሁንም ቢሆን ወደፊት እሳሳታለሁ ብዬ በመስጋት ዛሬ አውቄ ስሕተት አልሠራም፤ ስለዚህም ነገር ሳላበዛ ስለዓቢይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ያገኘሁትን መረጃ በመንተራስ በአጭሩ አቀርበዋለሁ፡…
• በአደባባይ በወያኔዎች ፊት ስለኢትዮጵያ ሕዝብ የተናገረው፣ ስለሥልጣን የተናገረው፣ አዲስና ግሩመረ ነው፤
• ወያኔዎች ተማሩ፣ አልተማሩ፣ በኢትዮጵያ ሀብት ከየኪዮስኩ የምስክር ወረቀቶች ቢገዙም በሃያ ሰባት ዓመታት ያልደረሱበትን የእውቀትና የማሰብ ደረጃ ዓቢይ ከነሱ ስር ሆኖ ባገኘው እውቀት ከመቀመጫው ሳይነሣ በለጣቸው፤ (አንድ ሌላ ወያኔ ያሠለጠነው ወደአሜሪካ ኮብልሏል፤ ) ባለሥልጣኖች ከተማሩበት አገዛዙን ከወደቀበት የአስተሳሰብ አዘቅት ያወጣው ነበር ፡፡
• ወያኔዎች ዓቢይን በጸጥታ ለመስማት መገደዳቸው ከገባቸውና ከተጠቀሙበት ትልቅ ትምህርት ነው፤
• ዓቢይ በወያኔ በራስ አለመተማመን ሕመም ላይ በእግሩ ቆመበት፡፡
• ዓቢይ ብቻውን አይደለም፤ ጓደኛ አለው፡፡
ዓቢይ አህመድና የኢትዮጵያ ፖለቲካ [ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም]
Filed in: Amharic