>

ኢትዮጵያ ማለት ትግራይ እና አዲስ አበባ ብቻ አለመሆናቸው ሊነገራቸው ይገባል (ብርሃነ መስቀል አበበ)

“የኦሮሞ ህዝብ ወደ ትግራይና አዲስ አበባ የሚወስዱ የኢንተርኔትና የመብራት መስመሮችን ወደ ማቆም ሊሸጋገር እንደሚችል ሊታወቅ ይገባል። ህወሃት በእሳት መጫወት ቢያቆም ለሱም ለአገርም ይበጃል። ትግራይና አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ያለመሆናቸው ቢነገራቸውም አይከፋም።”
ዘረኛው የህወሃት መራሽ አገዛዝ በኦሮሚያ የኢንተርኔት አገልግሎት በማቋረጥ
1ኛ፣ በኦሮሚያ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎችና ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ከሌሎቹ ክልሎች እንዲያሱና እንዲጎዱ ለማድረግ፣
2 ኛ፣ በኦሮሚያ ያሉ ሆቴሎችና የንግድ ተቋማት እንዲከስሩና ህዝቡ እንዲደሀይ፣
3ኛ፣ የኦሮሚያ ከተሞች ኢንተርኔትና መብራት የሌላቸው ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ እንዲሆኑ ለማድረግ፣
4ኛ፣ በኦሮሚያ ያሉ የመንግስትና አለም አቀፍ ድርጅቶች ሥራቸውን እንዳይሰሩና ከኦሮሚያ እንድሸሹ ለማድረግ፣
5ኛ፣ መላው የኦሮሞ ህዝብ የኢንተርኔት ተጠቃሚ እንዳይሆንና መረጃ እንዳያገኝ በማድረግ የኦሮሞ ህዝብን ለመጉዳት እያደረገ ያለውን ህገ ወጥና መድሎ የሞላበት ፓሊሲ ሳይውል ሳያድር ዛሬውኑ ካላነሳ የኦሮሞ ህዝብ ወደ ትግራይና አዲስ አበባ የሚወስዱ የኢንተርኔትና የመብራት መስመሮችን ወደ ማቆም ሊሸጋገር እንደሚችል ሊታወቅ ይገባል። ህወሃት በእሳት መጫወት ቢያቆም ለሱም ለአገርም ይበጃል። ትግራይና አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ያለመሆናቸው ቢነገራቸውም አይከፋም።
Filed in: Amharic