>

የኬንያ ባላስልጣናት ከኢትዮጵያ የሸሹትን የሞያሌ ስደተኞች ዛሬ ጎበኙ (እስራኤል ሰቦቃ)

የትግራይ ነጻ ኣዉጪ ፋሽስት ጦር ሞያሌ ዉስጥ የከፈተዉን ጭፍጨፋ በማምለጥ የኢትዮጵያን ድንበር በማቋረጥ ወደ ኬንያ ግዛት የገቡትንና ቁጥራቸዉ ወደ 10 ሺህ የሚጠጉትን የሞያሌ ስደተኞች የአስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸዉ መገለጹ ይታወቃል።
በመርሳቤት ምክትል ገዢ ጉቦ ጨዌ የተመራ ቡድን፤ የሞያሌ ኬንያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኣባል ቃልቻ ጉፉና የኣለም ኣቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ኣባላት ያሉበት ቡድን ስደተኞቹ ያረፉበትን መጠለያ ጎብኝቷል።
በገዛ ሃገራቸዉ የመኖር ህልዉናቸዉን ተነፍገዉና ከጭፍጨፋ በማምለጥ ወደ ጎሬቤት ሃገር የሽሹትን ዜጎች የጎሬቤት ሀገር ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና የግብረ ሰናይ ተቋማት ወደ ተጠለሉበት ስፍራ በመሔድ ጎብኝተዋል።
የአካባቢዉ የኬንያ ባላስልጣናት ላሳዩት ስብአዊ ትብብር መላዉ የኦሮሞ ህዝብ ከልብ ያመሰግናል።
Filed in: Amharic